Quantcast
Channel: Articles
Viewing all 139 articles
Browse latest View live

የሰበር ውሳኔዎች ግጭት

$
0
0

የሰበር ውሳኔዎች ግጭት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጥ የህግ ትርጉም ለበታች የክልልና የፌደራል ፍርድ ቤቶች አስገዳጅነት እንዲኖረው አስገዳጅ ህግ ከወጣ (አዋጅ ቁጥር 454/1997) ከአስር ዓመት ዓመት በላይ አልፎታል፡፡ በእነዚህ ሁሉ ዓመታት ውስጥ ህጉና አፈጻጸሙ ለፍትህ ስርዓቱ ያበረከተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ እና ያስከተለው ችግር በተመለከተ የዳሰሳና የክለሳ ጥናት ተደርጎ ውጤቱ ይፋ የሆነ ሪፖርት እስካሁን ድረስ የለም፡፡ እስከ አሁን ድረስ የህጉ አጠቃላይ ተቀባይነት መሰረት ያደረገው አሰራሩ ወጥነትን ያመጣል ከሚል በሀሳብ ደረጃ ሊያሳምን የሚችል አመለካከት እንጂ በተግባር ተፈትኖ እየታየ ያለ ሀቅ አይደለም፡፡

ተግባራዊ የመለኪያ ሚዛንን ለጊዜው ወደ ጎን እንተወውና ወጥነት የአዋጁ ዋና ዓላማና ግብ ነው ብለን እንነሳ፡፡ ችግሩ ግን ከዚህ ይጀምራል፡፡ አዋጅ ቁጥር 454/1997 ወጥነትን እንደ ዋና ሆነ ተጓዳኝ ዓላማና ግብ ይዞ ስለመነሳቱ በግልጽ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚናገር ድንጋጌ አልያዘም፡፡

በአዋጁ መግቢያ ላይ እንደተመለከተው የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር 454/1997 ሊወጣ የቻለው ስለፌደራል ፍርድ ቤቶች የወጣውን አዋጅ ቁጥር 25/88 (እንደተሻሻለ) እንደገና ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡ የአስፈላጊነቱ መሰረት ምን እንደሆነ በግልጽ የተመለከተ ነገር የለም፡፡

አዋጁ ዝምታን ቢመርጥም ህጉ ሊያሳካ የፈለገው ቀዳሚ ግብ የአገሪቱ ፍርድ ቤቶች በተመሳሳይ ጉዳይ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ወጥነት እንዲኖራቸውና ተገማች እንዲሆኑ ለማስቻል እንደሆነ ግምት ቢወሰድ በመርህ ደረጃ አሳማኝና አስማሚ ሀሳብ ነው፡፡ እንግዲህ ወጥነትና ተገማችነት የአገሪቱ የፍትህ ስርዓት ዋነኛው ገጽታ እንዲሆን ከታለመ ከብዙ ነገሮች መሐል ቢያንስ አንድ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታ ተሟልቶ ይገኝ ዘንድ ግድ ይላል፡፡ ይኸውም የሰበር ውሳኔዎች ራሳቸው ወጥነት ዐቢይ መገለጫቸው ሊሆን ይገባል፡፡ ግልጽ የአቋም ለውጥ በሌለበት በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ እርስ በእርስ የማይጣጣምና የሚጋጭ የህግ ትርጉም በሚኖርበት ጊዜ በበታች ፍርድ ቤቶች ላይ ውዥንብር በመፍጠር ተገማችነትን አደጋ ውስጥ ይከታል፡፡ አዋጅ ቁጥር 454/1997 ይፋ ህግ ሆኖ ከታወጀ ወዲህ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚሰጣቸው ውሳኔዎች ዓመት እየጠበቁ ከመታተማቸው ውጪ በአንድ ጉዳይ ላይ ተፈጻሚ የተደረገውን የህግ ትርጉም በቀላሉ መለየትና ማግኘት የሚያስችል የውሳኔዎች ጥንቅር (Codification) አሁን ድረስ አልተዘጋጀም፡፡ በዚህ የተነሳ በበታች ፍ/ቤቶች ይቅርና በራሱ በችሎቱ ዘንድ እንኳን ወጥነትን ማስፈን አልተቻለም፡፡

እርስ በእርስ ከሚጋጩ የሰበር ውሳኔዎች መካከል ለአብነት ያህል የሚከተሉት በአስረጂነት ይጠቀሳሉ፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ 47495 ያልታተመ እና ሰ/መ/ቁ. 47139 ቅጽ 11

በሰ/መ/ቁ 47495 ያልታተመ[1] ችሎቱ ህጉን በመተርጎም በደረሰበት ድምዳሜ መሰረት በሟች ስም ተመዝግቦ የነበረ የውርስ ሀብት በሽያጭ፣ በውርስ፣ በስጦታ ወይም በሌላ ህጋዊ መንገድ መተላለፉ ሳይረጋገጥ ውርሱ በሚጣራበት ጊዜ በአንደኛው ወራሽ ስም ተመዝገቦ እንደሚገኝ ከተረጋገጠ የውርሱ ሀብት ተደርጎ ሊጣራ አይገባውም፡፡ በዚህ ንብረት ላይ መብት አለኝ የሚል ወራሽ የባለቤትነት ምዝገባው ስርዓቱን ጠብቆ ያልተከናወነ ስለመሆኑ ሳያስረዳ እንዲሁም የባለቤትነት ምስክር ወረቀቱን ስልጣን ባለው አካል ሳያሰርዝ ንብረቱን በስሙ ያስመዘገበው ወራሽ እንዴት እንዳፈራው ሊረጋገጥ ይገባል በሚል የሚያነሳው ቅሬታ የሕግ መሰረት ያለው አይደለም፡፡

ሆኖም በሰ/መ/ቁ. 47139 ቅጽ 11[2] የተሰጠው የህግ ትርጉም በግልጽ እንደሚያስገነዝበን አንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት በስሙ የተመዘገበ ሰው ንብረቱ በእጁ እንዴት ሊገባ እንደቻለ ማስረዳት ካልቻለ ህጋዊ ወራሽ እንዳያስረክበው ሲጠይቅ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ 49239 ያልታተመ እና ሰ/መ/ቁ. 114669 ቅጽ 19

በአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ውስጥ በወንጀል የጥፋተኝነት ፍርድ ሳይኖር አንድ ሠራተኛ ለሰላሳ ወይም ከዚያ በላይ ቀናት ከታሰረ ውጤቱ ምንድነው? ለጥያቄው ምላሽ ከሰ/መ/ቁ 49239 ያልታተመ[3] አንጻር ካየነው ለአምስት ተከታታይ ቀናት ከስራ እንደቀረ ተቆጥሮ የሥራ ውሉ በህጋዊ መንገድ ይቋረጣል፡፡

ይሁን እንጂ በሰ/መ/ቁ. 114669 ቅጽ 19[4] ችሎቱ በሰ/መ/ቁ. 49239 ይዞት የነበረውን አቋም መሻሻሉን በግልጽ ሳይጠቁም የህጉን ትርጉም ቀይሮታል፡፡ በዚህ መዝገብ ተጠሪ የአመልካችን መኪና ሲያሽከረክሩ ግጭት በመከሰቱ ጉዳዩ እስኪጣራ ድረስ ለአራት ወር ከአስር ቀናት በጊዜ ቀጠሮ በእስር ከቆዩ በኋላ ዓቃቤ ህግ የወንጀል ክስ ለመቀጠል የሚያስችል ነገር ባለማግኘቱ መዝገቡን ዘግቶታል፡፡

ተጠሪ ከሰላሳ ቀናት በላይ ከስራ ቀርተዋል በሚል ከስራ ሲሰናበቱ የውሉን መቋረጥ አስመልክቶ ጉዳዩን ያዩት ፍርድ ቤቶች የእስራት ፍርድ ሳይኖር በጊዜ ቀጠሮ መታሰር የሥራ ውል ለማቋረጥ በቂ ምክንያት እንዳልሆነ ወጥ አቋም ላይ ደርሰዋል፡፡ የሰበር ችሎትም ከስር ፍ/ቤቶች አልተለየም፡፡ አከራካሪውን ጭብጥ አስመልክቶ ለህጉ በተሰጠው አስገዳጅ ትርጉም መሰረት፤

“በፍርድ ቤት ውሳኔ ከ30 ቀን በላይ ከስራ [መቅረቱ] ተረጋግጦ ያልተወሰነበት ሰራተኛ ያለማስጠንቀቂያ ከስራ ማሰናበት የአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 27 /1/በ/ ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ ያላገናዘበ ነው፡፡”

  1. ሰ/መ/ቁ. 25005 ቅጽ 5 እና ሰ/መ/ቁ. 26839 ቅጽ 5

የማይንቀሳቀስ ንብረት (መኖሪያ ቤት) ግንባታ ከጋብቻ በፊት ቢጀመርም ግንባታው የተጠናቀቀው ባልና ሚስት በጋብቻ ውስጥ በሚኖሩበት ጊዜ ውስጥ ከሆነ በተለይም አንደኛው ወገን ለቤቱ ግንባታ የገንዘብ አስተዋጽኦ አድርጎ ከሆነ በፍቺ ጊዜ ሁለቱም የቤቱን እኩል ድርሻ የማግኘት መብት እንዳላቸው የህግ ትርጉም የተሰጠው በሰ/መ/ቁ. 25005 ቅጽ 5[5] ነው፡፡ ይህ ትርጉም ግን ፀንቶ መቆየት የቻለው ለአንድ ሳምንት ያህል ብቻ ነው፡፡

ኀዳር 10 ቀን 2000 ዓ.ም. በሰ/መ/ቁ. 26839 ቅጽ 5[6] በተመሳሳይ ጉዳይ በተሰጠ የሰበር ውሳኔ መሰረት የማይንቀሳቀስ ንብረት (መኖሪያ ቤት) ግንባታ ከጋብቻ በፊት ተጀምሮ ባልና ሚስቱ በትዳር ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ከተጠናቀቀ በፍቺ ወቅት ለንብረቱ መገኘት ተጋቢዎቹ ያደረጉት አስተዋጽኦ ተመርምሮ እንደነገሩ ሁኔታ የግል ወይም የጋራ ሊባል ይገባል፡፡ ይህንንም ለመወሰን በንጽጽር ሲታይ አብዛኛው መዋጮ የተደረገው ከግል ነው ወይስ ከጋራ? የሚለውን ከግምት ማስገባቱ ተገቢ እንደሚሆን በውሳኔው ላይ ተመልክቷል፡፡ የንብረት ክፍፍሉን በተመለከተም ንብረቱ በአብዛኛው ከጋራ ሃብት መዋጮ የተገኘ ከሆነና የግል ንብረቱ ትንሽ ከሆነ ንብረቱ የጋራ ሆኖ እንደሚቆጠር፤ በንብረቱ ላይ የተቀላቀለውን የግል ሃብት በተቀላቀለው መጠን የግሉ የሆነው ተጋቢ ሊወስድ እንደሚገባ ከሰ/መ/ቁ. 25005 ያፈነገጠ አቋም ተይዞበታል፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ. 33200 ያልታተመ እና ሰ/መ/ቁ. 44025 ቅጽ 10

በሰ/መ/ቁ. 44025 ቅጽ 10 ንብረት በወራሾች በጋራ ከተያዘ የይርጋ ደንብ ተፈጻሚነትን እንደሚያስቀር ትርጉም ተሰጥቶበታል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት በሰ/መ/ቁ. 33200[7] በተሰጠ ውሳኔ ግን የጋራ ይዞታ ይርጋን ተፈጻሚ ላለማድረግ በምክንያትነት ሊጠቀስ እንደማይገባው ጠንካራ አቋም ተይዞበት ነበር፡፡ በዚህ ነጥብ ላይ የችሎቱ ሐተታ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

ንብረቱ በጋራም ተያዘ በተናጠል የተጠየቀው ዳኝነት የውርስ አጣሪ ተቋቁሞ ንብረት ለመከፋፈል እስከሆነ ድረስ ይሄው ጥያቄያቸው በሕግ በተቀመጠ የጊዜ ገደብ ካልቀረበ በይርጋ የማይታገድበት ምክንያት አይኖርም ጥያቄው ይርጋ የለውም ማለትም የይርጋን ዓላማ ውጤት አልባ ከማድረግ የተለየ አይሆንም፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ. 17937 ቅጽ 4 እና ሰ/መ/ቁ. 33200 ያልታተመ

በወራሽና ወራሽ መካከል የሚነሳ የንብረት ማስመለስ ክርክር በ3 ዓመት ይርጋ እንደሚታገድ በሰ/መ/ቁ. 17937 ቅጽ 4[8] እና በቀጣይነት ከተሰጡ በርካታ ውሳኔዎች መረዳት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ በሰ/መ/ቁ. 33200[9] አንድ በወራሽና ወራሽ መካከል የውርስ ይጣራልኝ አቤቱታ ላይ በሚያቀርበው ክስ ላይ ተፈጻሚነት ያለው ልዩ የይርጋ ድንጋጌ እንደሌለ ተጠቀሶ ይርጋው በፍ/ህ/ቁ. 1845 መሰረት በ10 ዓመት እንደሚታገድ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ. 32013 ቅጽ 6፣ ሰ/መ/ቁ. 44237 ቅጽ 10 እና ሰ/መ/ቁ. 40418 ቅጽ 10

የውርስ ሃብት ክፍፍል ጥያቄ በፍ/ብ/ሕግ ቁ. 1000/1/ በተመለከተው የሦስት ዓመትም ሆነ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 974/2/ በተቀመጠው የአምስት ዓመት የጊዜ ገደብ በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን በሰ/መ/ቁ. 32013 ቅጽ 6[10] ትርጉም ከተሰጠ ከሁለት ዓመት በኋላ ተመሳሳይ ይዘት ባለው ጉዳይ ግልጽ የአቋም ለውጥ ሳይደረግ የንብረት ክፍፍል ጥያቄ ይርጋ አያግደውም ተብሏል፡፡ በሰ/መ/ቁ. 44237[11] አመልካች የጠየቁት ዳኝነት ወራሽነታቸውን ማረጋገጣቸውንና የውርሱን ሀብት ተጠሪ ይዘው እየተጠቀሙበት በመሆኑ እንዲያካፍሏቸው ቢጠይቋቸው ፍቃደኛ ባለመሆናቸው የውርስ ሀብት አጣሪ በፍርድ ቤት እንዲሾምላቸው ነው፡፡ የሰበር ችሎት አመልካች የጠየቁት ዳኝነት የውርስ ሀብት ክፍፍል እንደሆነ በመጠቆም በፍ/ህ/ቁ. 1062 በማናቸውም ጊዜ ሊቀርብ የሚችልና በይርጋ የማይታገድ እንደሆነ በማተት የፍ/ህ/ቁ. 1000/1/ ድንጋጌን ተፈጻሚ በማድረግ የስር ፍ/ቤቶች ክሱን በይርጋ ውድቅ በማድረግ የሰጡትን ውሳኔ ሽሮታል፡፡

ጥቅምት 10 ቀን 2002 ዓ.ም. በተሰጠ ሌላ ውሳኔ ደግሞ የችሎቱን አቋም ለመጨበጥ አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ ከሰ/መ/ቁ. 40418 ቅጽ 10[12] የህግ ትርጉም መረዳት እንደሚቻለው የውርስ አጣሪው ባቀረበው ሪፖርት መሰረት የቀረበ የንብረት ልካፈል ጥያቄ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1080/3/ በተደነገገው የአንድ ዓመት የጊዜ ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፡፡

  1. ሰ/መ/ቁ. 08751 ቅጽ 6 እና ሰ/መ/ቁ. 93137 ቅጽ 15

የክልል ሰበር ሰሚ ችሎት ሐሰተኛ ማስረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ ሰጥቷል በሚል የዳግም ዳኝነት ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባው ለሰበር ችሎቱ ሳይሆን መጀመሪያ ፍርዱን ለፈረደው የስር ፍ/ቤት ነው፡፡ ይህ በሰ/መ/ቁ. 93137 ቅጽ 15[13] የተያዘው የችሎቱ አቋም በተመሳሳይ ጉዳይ በሰ/መ/ቁ. 08751 ቅጽ 6[14] ከተሰጠው ውሳኔ ጋር አብሮ አይሄድም፡፡ በዚህ መዝገብ ችሎቱ የሰጠው ውሳኔ በተጭበረበረ ሰነድ ላይ በመመስረት እንደሆነ በመግለጽ አመልካች ያቀረቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ግራ ቀኙን በማከራከር ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

[1] አመልካች ወ/ሮ ፈለቀች ሽፈራው እና ተጠሪ እነ ወ/ሮ በቀለች መንግስቱ /2 ሰዎች/ መጋቢት 20 ቀን 2002 ዓ.ም.

[2] አመልካች አቶ የሱፍ ሁሴን እና ተጠሪ አቶ አደን አብደላ ኅዳር 30 ቀን 2003 ዓ.ም.

[3] አመልካች የአ/አ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን እና ተጠሪ አቶ ፍቅሩ ከበደ የካቲት 3 ቀን 2002 ዓ.ም.

[4] አመልካች የኢትዮጵያ መንገዶች ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የደብረማርቆስ መንገዶች ጥገና ዲስትሪክት እና አቶ አስማረ ፈጠነ ጥቅምት 24 ቀን 2008 ዓ.ም.

[5] አመልካች መኮንን በላቸው እና ተጠሪ ወ/ሮ አለሚቱ አደም ኀዳር 3 ቀን 2000 ዓ.ም.

[6] አመልካች ወ/ሮ አስካለ ለማ እና ተጠሪ ሣህለ ሚካኤል በዛብህ ኀዳር 10 ቀን 2000 ዓ.ም.

[7] አመልካች አቶ አወል አማን እና ተጠሪዎች እነ አቶ ናሥር አማን /2 ሰዎች/ ያልታተመ ህዳር 11 ቀን 2001 ዓ.ም

[8] አመልካች ወ/ሮ ድንቄ ተድላ እና ተጠሪ እነ አቶ አባተ ጫኔ መጋቢት 20 ቀን 1999 ዓ.ም.

[9] ዝኒ ከማሁ

[10] አመልካች ደምስ ጥበበሥላሴ እና ተጠሪ ቴዎድሮስ ጥበበሥላሴ መጋቢት 25 ቀን 2000 ዓ.ም.

[11] አመልካች ወ/ሮ ሙለሸዋ ቦጋለ – በራሳቸውን እና ወኪል ለሆኑላቸው /4 ሰዎች/ እና ተጠሪ ወ/ሮ ፈልቃ ቤኛ ሰ/መ/ቁ. 44237 ቅጽ 10 መጋቢት 20 ቀን 2002 ዓ.ም.

[12] አመልካች ተስፋዬ ሞላ እና ተጠሪዎች እነ እሸቱ ሞላ /3 ሰዎች/ ጥቅምት 10 ቀን 2002 ዓ.ም.

[13] አመልካች ወ/ሮ ብጥር ታገለ እና ተጠሪ ወ/ሮ አገር ተሰማ የካቲት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.

[14] አመልካች ወ/ሮ አበበች በጅጋ እና ተጠሪ እነ ዶ/ር ተስፋዬ አካሉ /2 ሰዎች/ ግንቦት 26 ቀን 2000 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

የመቃወም አቤቱታ—የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

$
0
0

የመቃወም አቤቱታ —የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

1. ፍርድ መቃወም

ተካፋይ ባልሆነበት ክርክር የተሰጠው ውሳኔ መብቴን ይነካል በማለት አስቀድሞ ለአንድ ወገን የተሰጠውን ውሳኔ ለማሰረዝ በመቃወም አመልካች የሚቀርብ አቤቱታ

የመቃወም አቤቱታ ሲቀርብ ክርክሩ የሚካሄደው በመቃወም አመልካች እና አስቀድሞ በተሰጠው ውሳኔ ተጠቃሚ በሆነው የመቃወም ተጠሪ በሚባለው ወገን መካከል ሲሆን የዚህ ዓይነቱ ክርክር የሚቀርብበት እና የሚመራበት ስርዓት እንዲሁም የዚህ ዓይነቱን ክርክር የሚሰማው ፍርድ ቤት ስላለው ስልጣን በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ከቁጥር 358 እስከ 360 ተመልክቷል፡፡

የመቃወም አቤቱታው መቅረብ የሚገባው በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 222 እና 223 ድንጋጌዎች መሰረት ክስ እና የማስረጃ መግለጫ የሚቀርብበትን ስርዓት መሰረት በማድረግ ስለመሆኑ በግልጽ ተደንግጎአል፡፡

የመቃወም አቤቱታው እና የማስረጃው ቅጂ የመቃወም ተጠሪ ለሆነው ወገን እንዲደርስ መደረግ የሚገባው መሆኑን ከመግለጽ በስተቀር የመቃወም ተጠሪው የጽሁፍ መልስ እና የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ እንደሚገባው በእነዚህ ድንጋጌዎች ላይ በግልጽ የተጻፈ ባይሆንም የመቃወም ተጠሪ የሆነው ወገን በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 234 ድንጋጌ መሰረት ለቀረበበት የመቃወም አቤቱታ ያለውን የመከላከያ መልስ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚገባው ስለመሆኑ ከቁጥር 360(1) እና (2) ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በተለይም የመቃወሚያው ክርክር የሚሰማው የመጀመሪያው ክርክር በተሠማበት ስነ ስርዓት መሰረት ስለመሆኑ በቁጥር 360(2) የተመለከተው አስገዳጅ ድንጋጌ በቀጥታ የቀረበ ክስ እና ክርክር የሚስተናገድበትን ስርዓት በተመለከተ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕጉ የተመለከቱት መሰረታዊ ድንጋጌዎች የመቃወሚያ ክርክርን በማስተናገድ ረገድም በተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጻሚ ሊደረጉ የሚገባቸው መሆኑን በግልጽ የሚያስገነዝብ ነው፡፡

በዚህ ድንጋጌ የተመለከተው የክርክር አመራር ስርዓት ዓይነተኛ ዓላማ ሁለቱም ተከራካሪ ወገኖች እኩል ዕድል እንዲኖራቸው እና በተለይም የመቃወም አመልካች የሆነው ወገን የክርክሩ ተካፋይ ባልነበረበት ጊዜ የቀረበውን የመቃወም ተጠሪ ወገን የሰው እና የሰነድ ማስረጃ በመስቀልኛ ጥያቄ እና በማስተባበያ ክርክር ጭምር የመፈተን ዕድል እንዲያገኝ ለማስቻል እንደሆነ ይታመናል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 86398 ቅጽ 16፣[1] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 222፣ 223፣ 350-360

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 አንድ የክርክሩ ተካፋይ መሆን የሚገባው ሰው የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን ውሳኔ ተሰጥቶ ከሆነ እና ውሳኔውም ያረፈው በአንድ የክርክሩ ምክንያት በሆነ ንብረት ላይ ሁኖ ይህንኑ የክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገንን መብትና ጥቅም የሚነካ መሆኑ ከተረጋገጠ ፍርዱ ይኸው ወገን ባለበት እንዲታይና በሕግና በማስረጃ የተደገፈ ሁኖ ሲገኝ እንዲነሳለት የሚደነግግ ነው፡፡ አቤቱታው የሚቀርብበት ሥርዓትም በቁጥር 359 ስር በተመለከተው መንገድ መሆን እንደአለበት የተቀመጠ ሲሆን ይህ ድንጋጌ የመቃወሚያ አቤቱታ አቀራረብ በክስ አመሰራረት አይነት ሁኖ ማስረጃ ዝርዝር ሁሉ ይህንኑ ስርዓት ማሟላት እንደአለበት ያስገነዝባል፡፡ የዚህ ድንጋጌ ይዘቱና መንፈሱ ሲታይ ክርክሩ መኖሩን ከጅምሩ እያወቀ ውጤቱን በመጠበቅ ከፍርዱ በኋላ የፍርድ መቃወሚያ የሚያቀርበውን ወገን አቤቱታውን በመቀበል ለማስተናገድ አስፈላጊ ያለመሆኑን ሁሉ ያስገነዝባል፡፡

ይህም የክርክር አቀራረብ በቅን ልቦና የተመሰረተ ሁኖ በአነስተኛ ወጪ፣ ጉልበትና አጭር ጊዜ ፍትሐዊነት ያለውን ውሳኔ ለመስጠት የሚቻልበት አግባብ እንዲኖር እና ሕግ አውጪ ከፈለገበት አላማ ጋር መጣጣም ያለበት መሆኑም የሚታመን ነው፡፡ እንግዲህ አቤቱታውን የሚያቀርበው ወገን የቅን ልቦና ተከራካሪ ሁኖ መሰረታዊ መብቱን ማስከበር የሚችልበት የስነ ስርዓት ሕግ አግባብ እንዲኖር ሕግ አውጪ የፈለገ ሲሆን ይህንኑ መመዘኛ የሚያሟላ አቤቱታ አቅራቢ የሚቃወመው ፍርድ ዋጋ ያለው፣ ያልተፈፀመ መሆን እንደአለበትም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 ድንጋጌ ይዘት ያስረዳል፡፡ በሌላ አገላለፅ የፍርድ መቃወሚያ የሚቀርብበት ፍርድ ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ያልተሻረና አፈጻጸሙም ያልተጠናቀቀ ሊሆን እንደሚገባ ሕጉ ያሳያል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 93987 ቅጽ 17፣[2] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358፣ 359

የሟች ሀብት ተጣርቶ በክፍፍሉ ላይ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ውርሱ ሲጣራ ያልተሳተፈ የሟች ወራሽ ነኝ የሚል ወገን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358 መሰረት መቃወሚያ ማቅረብ ያለበት በውርስ አጣሪው ሪፖርትና ሪፖርቱን ባፀደቀው ፍ/ቤት ሳይሆን የክፍፍሉን ጥያቄ አይቶ ውሳኔ ለሰጠው ፍርድ ቤት ነው፡፡

የውርስ አጣሪ ሪፖርት በፍርድ ቤት መጽደቅ በራሱ ፍርድ ሁኖ ለአፈፃፀም የሚቀርብ ሣይሆን እንደማስረጃ የሚያገለግል ነው፡፡ በመሆኑም ሪፖርቱ የማስረጃነት ዋጋ አለው ከተባለ ደግሞ የክፍፍል ክርክር ሲቀርብ በማስረጃነቱ ላይ ክርክር ቢቀርብ ክርክሩ መቅረብ ያለበት በውርስ አጣሪና ሪፖርቱን በአፀደቀው ፍርድ ቤት ነው ተብሎ ውድቅ የሚሆንበት ሕጋዊ ምክንያት የለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 45905 ቅጽ 11፣[3] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358፣ ፍ/ህ/ቁ. 944፣ 946፣ 956፣ 960

ተከራካሪ ወገኖች በፍርድ ቤት የሚያካሂዱትን ሙግት በማቋረጥ የሚያደርጉት የእርቅ ስምምነት በፍርድ ቤት ትእዛዝ ተረጋግጦና ለሚመለከተው ክፍል ይተላለፍ መባሉ የፍርድ ያህል አስገጃጅነት ያለው በመሆኑ እርቁን ያፀደቀው ፍርድ ቤት እርቁ ለሕግና ለሞራል ተቃራኒ አይደለም በእርቁ መሠረት ይፈፀም በማለት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የሰጠውን ትእዛዝ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358 መሰረት በእርቅ ስምምነቱ መብቴ ተነክቷል በሚል ወገን ተቃውሞ ሊቀርብበት የሚችል ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 83582 ቅጽ 15[4]

2. ንብረት እንዳይያዝ

በአፈጻጸም ንብረት እንዳይያዝ፣ እንዳይታገድ በንብረቶቹ ላይ መብት አለኝ የሚል በክርክሩ ተሳታፊ ያልሆነ ሶስተኛ ወገን የሚያቀርበው አቤቱታ

የፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 418 ድንጋጌ አስፈላጊነት የክርክሩ አካል ያልሆኑና ፍርድ ያላረፈባቸው የ3ኛ ወገን ንብረት ሳይረጋገጥ ለፍርዱ ማስፈፀሚያነት እንዳይውሉ ለመከላከልና ባንጻሩ ፍርዱን የመፈፀም ለማስተጓጉል (እንዳይፈፀም ለሚቀርቡት በቂ ላልሆኑ አቤቱታዎችም) እልባት የሚሰጥ ነው፡፡ በመሆኑም በተያዙት ንብረቶች ላይ መብት አለኝ የሚል ወገን የሚያቀርበውን መቃወሚያና አቤቱታ ተቀብሎ መመርመር እንዳለበት የተጠቀሰው ድንጋጌም በግልፅ ያሰፈረው ነው፡፡ ይህ ከሆነ የዚሁ አንቀጽ 418(3) የአራተኛው ቅጂ ባለይዞታነትን ለማስረዳት የፅሁፍ ማስረጃ መቅረብ እንዳለበት የሚደነግግ ቢሆንም የእንግሊዘኛው ቅጂ የስነ- ስርዓት ህጉ ደግሞ ይህንኑ አንቀጽ ሲገልጽ The Claimant or 0bjector Shall adduce evidence to Show that and the date of the attachment he had Some interest in or was possessed of the property attached ይላል፡፡ እንግዲህ ከዚህኛው የእንግሊዘኛ ቅጂ የምንረዳው ማስረጃ በማቅረብ ለአፈጻጸም የቀረበውን ንብረት ማስረዳት እንደሚቻል የሚገልጽ ነው፡፡ የአማርኛው ቅጂም ቢሆን ከፍ/ህ/ቁ/1193 (1) እና (2) ድንጋጌዎች ጋር ተደምሮ ሲታይ ሌላውን የማስረጃ አይነት በግልጽ እንዳይቀርብ የከለከለው ሆኖ አይታይም፡፡

ሰ/መ/ቁ 97094 ቅጽ 17፣[5] ፍ/ህ/ቁ. 1193(1) (2)፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 418

በዋናው ክርክር የሚሰጠው ውሳኔ እና በውሳኔው መሠረት ለማስፈጸም የሚደረገው ሂደት የተለያዩ በመሆናቸው በሚቀርቡት መቃወሚያዎች ላይ የሚሰጡት ውሳኔዎችም የተለያዩ ናቸው፡፡ መቃወሚያ አቅራቢው መብቱ የተነካው በአፈጻጸም ሂደቱ ከሆነ ከአፈጻጸም ሂደቱ ጋር የተያያዘ መገፍትሄ ነው የሚሰጠው፡፡ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 418 መሠረት በሚቀርብ መቃወሚያ ላይ የሚሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 419 ተመልክቶአል፡፡ በዚህ መሠረት መቃወሚያው ተቀባይነት ያገኘ ከሆነ በአፈጻጸም የተያዘው ንብረት በከፊል ወይም በሙለ እንዲለቀቅ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ከዚህ አልፍ በአፈጻጸም የተያዘው ንብረት ለአንድ ወይም ለሌላው ተከራካሪ ወገን ይገባል የሚል ዳኝነት አይሰጥም፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ በዋናው ክርክር የተሰጠውን ውሳኔ የሚሽር ወይም የሚያሻሽል ውሳኔ አይሰጥም፡፡ የዚህ አይነት ውሳኔ መስጠት የሚቻለው ዋናውን ውሳኔ በመቃወም አቤቱታ ሲቀርብ ነው፡፡ ይህ ደግሞ እራሱን የቻለ የአቀራረብ ሥርዓት እና የክርክር አመራር ሂደት ያለው ነው፡፡ በዚህ ረገድ ተገቢው ድንጋጌም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 358 የተመለከተው ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 53607 ቅጽ 12[6]፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358፣ 418፣ 419

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 418 አግባብ የተሟላ ክርክርና ማስረጃ ያቀረበ ወገን አቤቱታው በመደበኛ ሙግት እንዲከናወን እንዳይጠይቅ ሕጉ ግልጽ ክልከላ ያላደረገበት ሲሆን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 421 ስር የተጠበቀው መብትም በሕጉ አግባብ የሚቀርቡ መቃወሚያዎች እንደተጠበቁ ሁነው አመልካቹ በምርጫው እንዲጠቀምበት የተቀመጠ እንጂ ይህንኑ ስርዓት እንዲከተል የግድ የሚደረግበት ያለመሆኑ ድንጋጌው በፈቃደኝነት የአቀራረፅ ስርዓት መቀመጡ አስረጂ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ 86133 ቅጽ 15[7]

የቀዳሚነት መብት አለኝ በሚል መቃወሚያ አቅርቦ ጥያቄው ውድቅ የተደረገበት ሰው በድጋሚ ክስ ማቅረብ የተፈቀደለት በአፈፃፀም ችሎት የንብረቱ ባለመብትነት በጭብጥነት ተይዞ በመደበኛው የሙግት ስርአት አይነት ከግራ ቀኙ ክርክርና ማስረጃ አንፃር ተመርምሮ ውሳኔ የሚሰጥበት ባለመሆኑ ይህንን እድል ለመስጠት ነው፡፡ አመልካቹ ይህንን መብት የሚያስከብርለት ሌላ ክስ የመሰረተ ከሆነ ግን የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 421 ክስ ለማቅረብ ስለሚፈቅድ ብቻ በተመሳሳይ ጉዳይ ዳግመኛ ክስ ማቅረብ የስነ-ስርአት ህጉ አላማ አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 37214 ቅጽ 9፣[8] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 421

 

 

 

[1] አመልካች ወ/ሮ አሰለፈች ይመር እና ተጠሪዎች እነ ወ/ሮ አስመረት ተወልደ /3 ሰዎች/ ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.

[2] አመልካች እነ አቶ ዳንኤል ወንዳፈራ /2 ሰዎች/ እና ተጠሪ እነ ወ/ሮ አስናቀች ቦጋለ /4 ሰዎች/ ሐምሌ 18 ቀን 2006 ዓ.ም.

[3] አመልካች ሚስስ ሚላን ፑሲጂ /2 ሰዎች/ እና ተጠሪ እነ ሐንድሬ ፒስ ማልጂ /2 ሰዎች/ ጥቅምት 3 ቀን 2003 ዓ.ም.

[4] አመልካች ወ/ሮ ወርቅነሽ ውብነህ ተጠሪዎች እነ ወ/ሮ አልማዝ ዓለሙ /3 ሰዎች አንደኛው በሌሉበት/ መጋቢት 27 ቀን 2005 ዓ.ም.

[5] አመልካች ወ/ሮ አስቴር አምባው እና ተጠሪዎች እነ አቶ አበባው ክፍሌ /2 ሰዎች/ ህዳር 8 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም.

[6] አመልካች የምጥን መንደር መኖሪያ ቤቶች የህብረት ሥራ ማህበር እና ተጠሪዎች እነ ወ/ሮ ባየች አይገምት /3 ሰዎች 2 ሰዎች በሌሉበት/ ህዳር 14 ቀን 2003 ዓ.ም.

[7] አመልካች እነ አቶ ፍቅሩ ከበደ /11 ሰዎች/ እና ተጠሪ ወ/ሮ አስቴር አርአያ /2 ሰዎች/ ጥቅምት 20 ቀን 2006 ዓ.ም.

[8] አመልካች አቶ ተስፊዬ አለሙ እና ተጠሪ እነ ሐጂ ይማም ሙዘይን /3 ሰዎች/ የካቲት 25 ቀን 2002 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

ዳግም ዳኝነት—የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

$
0
0

ዳግም ዳኝነት—የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

የመጨረሻ ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ ውሳኔው ወይም ትዕዛዙ ሐሰተኛ ማስረጃን መሰረት በማድረግ መሰጠቱ ሲረጋገጥ ጉዳዩ በድጋሚ /እንደገና/ የሚታይበት ስርዓት

በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 6(2) ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል የመጨረሻ ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ ውሳኔው ወይም ትዕዛዙ የተሰጠው በሃሰት ተዘጋጅቶ የቀረበ ሰነድን፣ ሃሰተኛ የምስክርነት ቃልን፣ ወይም መደለያን ወይም ወንጀል ጠቅሶ የሆነ ተግባርን መሰረት አድርጎ መሆኑን አቤት ባዩ ሲረዳው ጉዳዩ በይግባኝ ከመታየቱ በፊት[1] ውሳኔውን የሰጠው ፍ/ቤት ራሱ ዳኝነቱን በድጋሚ እንዲያይ ጥያቄ ለማቅረብ መብት የሚሰጠው ነው፡፡ የድንጋጌው ሙሉ ይዘትና መንፈስ የሚያሳየው የመጨረሻው ፍርድ ከተሰጠ በሁዋላ ሀሰተኛ ሰነድ ወይም ሀሰተኛ የምስክርነት ቃል ወይም መደለያ እንደተደረገና አቤት ባዩም ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት አስፈላጊውን ትጋት አድርጎ ለማወቅ ያለመቻሉን በሚገባ ለማስረዳት የሚችል የሆነ እንደሆነ፣ እነዚህ ጉዳዮች መኖራቸው ወይም መፈጸማቸው ታውቆና ተገልጾ ቢሆን ኖሮ ለፍርድ መለወጥ ወይም መሻሻል በቂ ምክንያት ሊሆኑ ይችል እንደነበር ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ፣ የተሰጠ ፍርድ ሊያስለውጥ የሚችል አዲስ ማስረጃ ማግኘቱ ብቻ ፍርድ እንደገና እንዲታይ የማያደርግ መሆኑን፣ ማስረጃው ፍርዱን በማሳሳት ውጤቱን ያበላሸና ተገቢ ያልሆነ ድርጊትን የሚያሳይ መሆን ያለበት መሆኑን ነው፡፡

በመሆኑም ማስረጃው በሐሰት ተዘጋጅቶ የቀረበ ሰነድን፣ ሀሰተኛ የምስክርነት ቃልን ወይም መደለያን ወይም ወንጀል ጠቀስ ተግባርን መሰረት ያደረገ መሆንና ማስረጃው ፍርዱ በሚሰጥበት ጊዜ ፍርዱ እንደገና ይታይልኝ የሚለው ተከራካሪ ወገን ማስረጃው መኖሩን ያውቀው የነበረ ያለመሆኑ፣ ይግባኝ ቀርቦበት ከሆነ አዲስ ማስረጃው ለይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ውሳኔ በሚሰጥበት ጊዜ ግምት ውስጥ እንዲያስገባ ይግባኙ ለቀረበለት ፍርድ ቤት መቅረብ ያለበት መሆኑ፣ የተገኘው አዲስ ማስረጃ የሀሰት ሰነድን፣ ሀሰተኛ ምስክርነትን፣ መደለያንና የመሳሰሉትን የሚመለከት ለመሆኑ ማረጋገጫ መኖሩን በሚጠቅስ ቃለመሐላ የተደገፈና ማስረጃው አስፈላጊው ትጋት የተደረገበት ቢሆንም ፍርዱ በተሰጠ ጊዜ በአመልካቹ ያልታወቀ መሆኑን የሚገልፅ መሆን ያለበት መሆኑ በቅድመ ሁኔታነት ሊሟሉ የሚገባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ድንጋጌው ያስገነዝባል፡፡

የዳግም ዳኝነት ጥያቄ ጥብቅ መለኪያዎች ያሉት መሆኑን ከድንጋጌው ይዘት መንፈስ መገንዘብ የምንችለው ጉዳይ ሲሆን የድንጋጌው ጥብቅ የመሆን አይነተኛ አላማም የተሰጡ ውሳኔዎችን አጣራጣሪነት ለማስወገድ መሆኑ ይታመናል፡፡ ስለሆነም የዳግም ዳኝነት ጥያቄ የቀረበለት ፍርድ ቤት ለውሳኔው መሰረት የሆነው ሰነድ ወይም ማስረጃ ሐሰተኛ መሆኑን ብቻ ሳይሆን በሕጉ የተመለከቱት ሁሉም መመዘዎችን አቤቱታ አቅራቢው ማሟላቱን በቅድሚ ሊያረጋገጥ ይገባል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 104028 ቅጽ 17፣[2] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 6

ፍርድ በድጋሚ እንዲታይ የሚጠይቅ ሰው ሀሰተኛ መረጃ የተሰጠው መንግስት በኃላፊነት ቦታ ላይ ባስቀመጠው ባለስልጣን እና በመንግስት አካል መሆኑን ከማስረዳት አልፎ የመንግስት ባለስልጣን ይህንን ህገወጥ ተግባር የፈፀመበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ሊጠየቅ አይገባውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 91968 ቅጽ 15፣[3] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 6፣ ወ/ህ/ቁ. 403፣ 405

የተፈጻሚነት ወሰን

አንድ ተከራካሪ ጠበቃ ወክሎ እንዲከራከር እንጂ የውርስ ሀብት ንብረት ስምምነት ለማድረግ የውክልና ስልጣን አልተሰጠውም በሚል ዳግም ዳኝነት እንዲታይ የሚቀርብ አቤቱታ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 6 ስር አይሸፈንም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 45839 ቅጽ 9[4]

የማስረዳት ግዴታ

በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 6(1)(ሀ) መሰረት ጉዳዩ እንደገና እንዲታይ የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት የሚኖረው የመጨረሻው ፍርድ ወይም ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ የተሰጠው በሐሰት ተዘጋጅቶ የቀረበውን ሰነድ ወይም ሀሰተኛ የምስክርነት ቃልን ወይም መደለያን ወይም ወንጀል ጠቀስ የሆነ ተግባርን መሰረት በማድረግ ሲሆን አቤት ባዩም ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት አስፈላጊውን ትጋት አድርጎ ለማወቅ አለመቻሉን ማስረዳት የሚጠበቅበት ከመሆኑም በላይ በፊደል (ለ) እንደተጠቀሰውም እነዚህ የተዘረዘሩት ተግባሮች መፈጸማቸው ቢገለጽ ኖሮ ለተሰጠው ፍርድ መለወጥ ወይም መሻሻል በቂ ምክንያት ሊሆኑ ይችሉ እንደነበር አቤት ባዩ የማስረዳት ኃላፊነት አለበት፡፡

ሰ/መ/ቁ 89641 ቅጽ 15[5]

የሚቀርብበት ጊዜ

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሔ/ቁ. 6 ተጨባጭ ውጤት ሊሰጥ በሚችል አኳኋን ሊተገበር የሚችለው ውሣኔው ሐሰተኛ እና ወንጀል ጠቀስ የሆኑ ተገባሮችን መሰረት በማድረግ የተሰጠ ነው የሚል አቤቱታ እስከቀረበበት እና በቂና አሣማኝ መሆኑን ፍ/ቤቱ እስካመነበት ድረስ ይግባኝ ይባልበትም አይባልበትም ያለልዩነት ሥራ ላይ እንዲውል በሚያስችል ሁኔታ ሲተረጎም ነው፡፡

ዳኝነት እንደገና እንዲታይ (Review of judgement) በሚል የሚቀርብ አቤቱታ አስቀድሞ በተሰጠ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የተባለበት ነው በሚል ምክንያት ብቻ ውድቅ ሊደረግ እንደሚገባ ሰ/መ/ቁ. 16624 ተሰጥቶ የነበረው ትርጉም ተለውጧል፡፡ ስለሆነም ጥያቄው ጉዳዩ በይግባኝ ታይቶ ውሳኔ ከተገኘ በሁዋላም ቢሆን በቁጥር 6 ስር የተመለከቱት መመዘኛዎች ተሟልተው እስከተገኙ ድረስ መቅረብ ይችላል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 43821 ቅጽ 15[6]

የሚቀርብበት ፍርድ ቤት

ማንኛውም ውሳኔ የተሰጠበት ሰው በፍ.ስ.ስ.ሕ.ቁ. 6(1)(ሀ) እና (ለ) ስር የተመለከቱትን ሁኔታዎች ወይም ከእነዚህ አንዱን መሰረት በማድረግ የዳግም ዳኝነት አቤቱታውን ማቅረብ የሚችለው ፍርዱን ለፈረደው ወይም ትዕዛዙን ወይም ውሳኔውን ለሰጠው ፍ/ቤት ስለመሆኑ በፍ.ስ.ስ.ሕ.ቁ. 6(1) ስር በግልጽ ተመልክቶአል፡፡

የክልል ሰበር ሰሚ ችሎት ሐሰተኛ ማስረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ ሰጥቷል በሚል የዳግም ዳኝነት ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባው ለሰበር ችሎቱ ሳይሆን መጀመሪያ ፍርዱን ለፈረደው የስር ፍ/ቤት ነው፡፡

የፍ.ስ.ስ.ሕ.ቁ. 6 ዓይነተኛ ዓላማ ተገቢ ሁኔታዎችና ፍሬ ነገሮች ተሟልተው መገኘታቸው ሲረጋገጥ በሀሰተኛ ማስረጃ፣ በመደለያና በመሰል ወንጀል ጠቀስ ድርጊቶች ምክንያት የተዛነፈውን ፍትሕ ወደነበረበት መመለስ ነው፡፡ ይህ ሂደት ከሰበር ችሎቶች የስልጣን ወሰን ውጪ የሆነው ፍሬ ነገርን የማጣራት እና ማስረጃን የመመዘን ተግባራት የሚከናወንበት በመሆኑ ምክንያት በሰበር ችሎት ሊስተናገድ የሚችልበት የህግ አግባብ ባለመኖሩ የተጠቀሰውን የስነ ስርዓት ድንጋጌ ዓላማ ለማሳካት ይቻል ዘንድ የሚኖረው አማራጭ የዳግም ዳኝነት አቤቱታው ፍሬ ነገር የማጣራት እና ማስረጃ የመመዘን ተግባራትን የማከናወን ስልጣን ባላቸው የስር ፍ/ቤቶች እንዲስተናገድ ማድረግ ይሆናል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 93137 ቅጽ 15[7]

ማስታወሻ

የችሎቱ አቋም በተመሳሳይ ጉዳይ በሰ/መ/ቁ. 08751 ቅጽ 6[8] ከሰጠው ውሳኔ ጋር አብሮ አይሄድም፡፡

በዚህ መዝገብ ችሎቱ የሰጠው ውሳኔ በተጭበረበረ ሰነድ ላይ በመመስረት እንደሆነ በመግለጽ አመልካች ያቀረቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ግራ ቀኙን በማከራከር ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ምንም እንኳን እንደገና እንዲታይ አቤቱታ የቀረበበት የችሎቱ ውሳኔ ተጭበረበረ በተባለው ሰነድ ይዘት ላይ ተመርኩዞ ባለመሰጠቱ የተነሳ አቤቱታው ውድቅ ቢደረግም በሰ/መ/ቁ. 93137 ከተያዘው አቋም አንጻር አቤቱታው ከጅምሩ ሊስተናገድ የሚገባው አልነበረም፡፡

ይግባኝ

ዳኝነት በድጋሚ እንዲታይ በሚቀርብ አቤቱታ ዳኝነቱ በድጋሚ ሊታይ አይገባውም ወይም ይገባዋል? በማለት ፍርድ ቤቱ በሚሰጠው ትዕዛዝ ወይም ብይን ላይ ይግባኝ ማቅረብ አይቻልም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 42871 ቅጽ 9፣[9] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 6(3) እና (4)

 

[1] በሰ/መ/ቁ 43821 (አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን እና ተጠሪ አቶ አማረ ገላው ሐምሌ 30 ቀን 2002 ዓ.ም. ሰ/መ/ቁ. 43821 ቅጽ 9) ዳኝነት እንደገና እንዲታይ ጥያቄው መቅረብ ያለበት ከይግባኝ በፊት እንደሆነ በሰ/መ/ቁ 16624 ተሰጥቶ የነበረው የህግ ትርጉም ተለውጦ ከይግባኝ በኋላም ሊቀርብ እንደሚችል አቋም ተይዞበታል፡፡

[2] አመልካች ወ/ሮ ብዙአየሁ ያለው እና ተጠሪ አቶ ሲሳይ ካሴ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.

[3] አመልካች አቶ ግርማ ሰንበት አልቀረቡም እና ተጠሪ፡- ወ/ሮ አልማዝ ገብረየስ ታህሳስ 15 ቀን 200 ዓ.ም.

[4] አመልካች ወ/ሮ ይርጋአለም ከበደ ድና ተጠሪ እነ ወ/ሮ ፅጌ ሚካኤል / 5 ሰዎች/ ሚያዝያ 5 ቀን 2002 ዓ.ም

[5] አመልካቾች እነ ወ/ሮ ሐረገወይን ብርሃኑ /2 ሰዎች/ እና ተጠሪዎች እነ ወ/ሮ አዜብ ብርሃኑ /2 ሰዎች/ ጥቅምት 21 ቀን 2006 ዓ.ም.

[6] አመልካች ወ/ሮ ትርሐስ ፍስሐዬ እና ተጠሪ ወ/ሮ ዘነበች በሪሁን ጥር 5 ቀን 2002 ዓ.ም.

[7] አመልካች ወ/ሮ ብጥር ታገለ እና ተጠሪ ወ/ሮ አገር ተሰማ የካቲት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.

[8] አመልካች ወ/ሮ አበበች በጅጋ እና ተጠሪ እነ ዶ/ር ተስፋዬ አካሉ /2 ሰዎች/ ግንቦት 26 ቀን 2000 ዓ.ም.

[9] አመልካች የቀድሞ ወረዳ 07 ቀበሌ 32 አስተዳደር ጽ/ቤት እና ተጠሪ ወ/ሮ ጆሮ ዋቅጅራ ጥር 12 ቀን 2002 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

THE HISTORY AND TRADITION OF JUDGMENT AND JUDGMENT WRITING IN ETHIOPIA

$
0
0

Taken from: Judgment Writing Teaching Material

Prepared by: Misker Getahun & Tafese Yirga

Prepared under the Sponsorship of the Justice and Legal System Research Institute

2009

THE HISTORY AND TRADITION OF JUDGMENT AND JUDGMENT WRITING IN ETHIOPIA

For the prime reason that there is no adequate source material to deal with the entire history and tradition of judgment and judgment writing in Ethiopia only, a brief account of discussion on the topic will be made in the forthcoming section. As such, the discussion will be based on the period from the reign of Emperor Zar’a Ya’eqob,(1434-1468) which marked the end of monarchical rule and the beginning of a new era.

In the legal history of Ethiopia, the first codified law of the country is coined with the name Zar’a Ya’eqob, who directed the compilation of the then existing legal norms by and through the Ethiopian Orthodox Church scholars. This law was known as “Fewuse Menfesawi”, which has the literal meaning of “spiritual remedies”. The contextual translation of same is “cannonical penances.” Emperor Zar’a Ya’eqob was not only the reason for the compilation of the then existing legal norms of the country in to a code,but he is also credited for making an order which resulted in the bringing of the copy of the so called “Fetha Negest” (the law of the kings) from Egypt and had it translated in to Ge’ez, which was the then working language of the country.

Another incident which has a historical as well as legal significance in the country came at the year 1931, which unfolded the promulgation of the first written constitution of Ethiopia by virtue of the then reigning Emperor of the country, Haile Sellasie I, whichestablished a two -chamber parliament (members of which were appointed by himself).

In between these great historical incidents i.e., the promulgation of the first ever written constitution of 1931 and the compilation of the ‘fewuse menfesawi’ oral as well as some foreign travelers’ travel memories (diaries) give evidence to the fact that the people of Ethiopia, then administered by local chiefs and tribe leaders, having their own small area to administer, were subjected to a particular norms and custom that were prescribed by the chief of the society.

Emperor Haile Sellasie I had replaced the 1931 Constitution by enacting the Revised Constitution in 1955 which among others came up with one of the chambers of parliament as elective body. In addition to these, the Emperor had managed to have promulgated six new modern law codes all between the years 1957 and 1965. These include; the civil code, the civil procedure code, the penal code, the criminal procedure code, the commercial code and the maritime code.

Basically there are two main criteria of identifying laws in to the three major legal families in the world: namely the Romano Germanic (Romanistic-German) family, the common Law family, and the socialist family. These are: the criteria of ideology (which is the product of religion, philosophy, or political, economic or social structure) and the criteria of legal technique.

Generally speaking, the major sources of the codified laws of Ethiopia seems to be the codes of continental or civil law systems, most of which were based on Roman law and jurisprudence. These western laws and jurisprudence, i.e., the Romanistic-German, were believed to have been transplanted in the Ethiopian legal system through reception when Ethiopia accepted the “Fetha Negest” in the fifteenth century, which was mostly based on Roman-Byzantine law.

However, it is important to say a few words, at this juncture, concerning the nature and application of laws in the country prior to the coming into force of the codified laws. Especially before 1936, cases were entertained in Ethiopia on the basis of the then existing customary laws, which could be different at different localities, and on natural law. Natural law, mainly, referred to be a moral law, has its basis on natural justice. It, originally, was meant to refer to a law of common-sense which could be applied by any reasonable person within a given society. Later, it was developed and elaborated so as to have application in light of religious edicts. Thus, it must be noted here that there was an administration of justice in the country even in the absences a written provision of law made by the state.  In the above mention has been fairly made with regard to the existence of applicable laws in the distant past as well as their nature and the source they were taken from. Apart from these, it is necessary to investigate in to the overall administration of justice and the manner of rendering and writing of judgment in Ethiopia, as a whole.

With respect to administrating justice in Ethiopia prior to 1936, it can be said that Ethiopians have a rich culture of participating in the administration of justice. This holds true, as it was considered as a “Civic duty” to take part in the administration of justice on the part of the people.

In the past, cases were used to be brought before any person in the locality and the person for whom the case is submitted for resolution was required to adjudicate as a judge or settle as an arbitrator. This kind of settlement of dispute was designated by foreigners as a “Road-Side-Court”. The person so requested would hear the dispute in the presence of people who happened to be there and finally decide the case as his conscience dictated him. If he found the case submitted to him for disposal is, however, complicated he would take the disputants himself or send them to the court of first instance by tying their clothes together, where the case was then made to be resolved (decided) in accordance with the customary law of the locality.

Hence, it should be underlined here that judgments given during these times were solely based on the personal appreciation of facts and on a person’s individual conception of justice. And customary laws, which mean without the existence of a written law, and more importantly the judgments, were given orally. As such, it appears difficult to deal with the features of the judgments being rendered then.

It is the year 1942 which heralded the coming in to existence of a structured court system in the history of the Ethiopian legal system. The Administration of justice proclamation of 1942, March 30, had also established a four-tier court system which later added the governor-general, sub-district and local judge courts.  A court of this nature had been exercising both civil and criminal jurisdictions within the same territorial limit.

By virtue of the administration of justice proclamation on March, 1942, there were created five hierarchically arranged courts in Ethiopia. These are, in accordance with their hierarchy from bottom to top, Yafer-Dagna or Yessir Dagna (court of first instance), yakal Dagna (district court), Shaleqa court (provincial court), the court of Afe-Negus (Appellate court of the chief justice) and finally the Zufan chilot (Crown court) where the emperor himself preside.

In the early times judges used to adjudicate cases in the name of the emperor or king of the state as the emperor was thought to be the fountain of justice and the judges were called “Afe-Negus” which literally means the mouth of the king. As such, the conceptual thinking embodied in the decisions rendered by judges was considered to show some principles of law. Such norms of both substantive and procedural laws were referred to as “Atse-Ser’at”. which has the meaning of presidential jurisprudence that developed out of case law or judge-made-law. Of course, the basis for this Atse Ser’ at law was judgment. When a case is decided at a local level and endorsed by a national court of appeal, the ruling becomes, from that moment on wards, king’s rule or Atse-Ser’ at. As such, it could be cited in the future as law in deciding cases of similar nature.

However, Case law, unlike other Ethiopian laws, is not found in an adequate quantity being recorded in a case digest in Ethiopia. Hence, it poses difficulty so as to illustrate the nature and characteristic features of judgments rendered in the past. As a result, due to the lack of recorded written judgments rendered in the previous period, it becomes impossible to evaluate the judgments given during the past However, there are a few decisions known to the society through various means, especially historical tales, and literature. Let’s see the features of some of these decisions.

Among other things, finding of truth, weighing of evidence, due process of law, equity and fairness can be mentioned as a basic tenet of those judgments. However, since it is only the report of the case and the judgment that is accessible, so far, more cannot be said on the issue of judgment and judgment writing at this level.

Therefore, by way of summary, it can be said that only little is known and hence few things can be said about the history of judgment and judgment writing due to the simple reason that there are not adequate recorded written judgments rendered in the past.

 


Filed under: Articles

ሶስተኛ ወገን ተከሳሽ—የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

$
0
0

ሶስተኛ ወገን ተከሳሽ—የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

ከተከሳሽ ጋር ኃላፊነት ሊወስድ ወይም ሊካፈል የሚችል ሦስተኛ ወገን በተከሳሽ ጠያቂነት በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወደ ክርክሩ የሚገባ ተከራካሪ

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 43/1/ “…ሌላ ሦስተኛ ወገን ከእኔ ጋር ድርሻ ካሣውን መክፈል አለበት…” በሚል ይቀመጥ እንጂ ከዚህ የሕግ አነጋገር ድርሻ ካሣውን የሚለውን ሐረግ ካየነው ትርጉም የሚሰጥ መስሎ አይታይም፡፡ ለምን ቢባል ድርሻ እና ካሣ የተለያዩ ፅንሰ ሃሳቦች ናቸው፡፡ አንዱ ቃል ሌላውንም ሊተካ አይችልም፡፡ ምንጫቸውም የተለያየ ነው፡፡ በተለይም “Where a defendant claims to be entitled to contribution or indemnity from any person . . .” ከሚለው የዚሁ ድንጋጌ የእንግሊዘኛ ግልባጭ ጋር ከላይ የተመለከተውን ሐረግ ከተመለከትነው “ድርሻ” እና “ካሣ” የተለያዩ ሆነው “ወይም” በሚለው ምህፃረ ቃል የተያያዙ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ድርሻ (Contribution) የሚለው ቃል ለክሱ ምክንያት በሆነው ጉዳይ ከተከሳሹ ጋር የአንድነትና የነጠላ ግዴታ ያለባቸው ወገኖች ኖረው ከሳሽ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1897 መሠረት አንደኛውን ባለዕዳ ብቻ ነጥሎ በከሰሰ ጊዜ ተከሳሹ ከእኔ ጋር ድርሻውን መክፈል ያለበት ሌላ ሦስተኛ ወገን ስላለ የክርክሩ ተካፋይ ይሁንልኝ በማለት በሚያቀርበው ጥያቄ መሠረት የክርክሩ ተካፋይ እንዲሆን በማድረግ፤ እንዲሁም ካሣ (indemnity) የሚለው ቃል ደግሞ ተከሳሹ በተከሰስኩበት ጉዳይ ኃላፊ የምሆን ከሆነ የሚፈረድብኝ ክፍያ እኔን ተክቶ የሚሸፍን ወገን /እንደ ኢንሹራንስ ባለ ጉዳይ/ ስለአለ ጣልቃ ገብቶ ይከራከራር በማለት የክርክሩ ተካፋይ እንዲሆን በማድረግና የሚመለከታቸው ወገኖች በአንድ ፋይል እንደተገናኙ ጉዳዩ የሚያልቅበትን ሥርዓት በመዘርጋት ተከታይ ክስን ለማስቀረት ታስቦ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንረዳለን፡፡

ይህ ባይሆን ኖሮ ድርሻ የሚከፍል ወገን እያለ ከተከሳሽ ላይ ብቻ ሲፈረድበት እርሱም በተራው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1908 እና 1909 መሠረት በብልጫ በከፈለው መጠን በሌሎች የጋራ ባለእዳዎች ላይ ክስ ማቅረቡ አይቀሬ ይሆናል፡፡

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 43 አስፈላጊነት ተከታይ ክስ ሳይኖር በክርክርና በማስረጃ አቀራርብ ረገድ ጉዳዩን በአንድ ፍ/ቤት እንዲታይ በማድረግ ኃላፊነት ያለባቸውን እና ሊከፈል የሚገባውን የካሣ መጠን በመወሠንና በመጨረሻም የሚከፍለውን ወገን በመለየት በአጭር ጊዜ በአነስተኛ ወጭ እልባት እንዲያገኝ ለማድረግ ነው፡፡

በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 43/2/ ሦስተኛው ወገን በክሱ ውስጥ እንዲገባ ፍ/ቤቱ የፈቀደ እንደሆነ የክሱ ማመልከቻ ግልባጭና ለክሱ የተሠጠው የመከላከያ መልስ እንዲደርሰው ይታዘዛል ተብሎ ከተደነገገው “…በክሱ ውስጥ እንዲገባ…” የሚለው ሐረግ ይህ ሦስተኛ ወገን የክርክሩ ተካፋይ እንዲሆን መደረጉንና የክርክሩ ተካፋይ (a party to the suit) ከሆነም ስለ ጉዳዩ የሚያቀርበው ክርክር ድርሻ ወይም ካሣ ክፍያ የመክፈል ግዴታ ያለበት መሆኑን በሚመለከት ክርክር ካለው ከተከሳሽ ጋር ክርክር ለማድረግ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ከሳሹ ያቀረበውን ክስ አስመልክቶ በኃላፊነትና በካሣ መጠን ረገድ ክርክር ማቅረብ የሚችል መሆኑን አመልካች ነው፡፡

የክሱ ማመልከቻና ለክሱ የተሰጠው የመከላከያ መልስ እንዲደርሰው የሚደረገውም የሦስተኛ ወገን ተከሳሹ ክርክር እንደአስፈላጊ’ቱ ከተከሳሹ ጋር ሊሆን እንደሚችልና በተካሹ እንደተገለፀው ድርሻ ወይም የካሣ ክፍያ ካለበት ደግሞ ተከሳሹ ለከሣሽ ኃላፊነት አለበት ወይስ የለበትም? ካለበትስ ለደረሰው ጉዳት ሊከፈል የሚገባው የካሣ መጠን ምን ያህል ነው የሚለውን በሚመለከት በተከሳሽ እግር ተተክቶ ከከሳሹ ጋር መሟገት እንዲችል ነው፡፡ በዚሁ በቁጥር 43/2/ “…በክሱ ውስጥ እንዳለ ይቆጠራል” የሚለውና የዚህ ግልባጭ የሆነው የእንግሊዝኛው ንባብ “…shall be deemed to be in the same position as a defendant” የሚለው አነጋገር ይህንኑ አባባል የሚደግፍ ነው፡፡

እንዲሁም ይህ ሦስተኛ ወገን ተከሣሽ ቀርቦ በክርክሩ ውስጥ ገብቶ እንዲከራከር ጥሪ ተደርጐለት ያልቀረበ እንደሆነ ምን ውጤት እንደሚያስከትል በሚደነግገው በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁጥር 76 ላይ፤

“…ይህ ሦስተኛ ወገን ቀርቦ በክርክሩ ውስጥ በመግባት መልስ እንዲሰጥ ፍ/ቤቱ አዞ መጥሪያው ከደረሰው በኋላ ቀርቦ መልስ ሳይሰጥ ወይም አላፊ የማይሆንበትን ምክንያት በማስረዳት ሳይከራከር የቀረ እንደሆነ…” /ሰረዝ የተጨመረ/

የሚለውን የሕግ አነጋገር፤

“Where a third party duly summoned to appear under Art. 43(2) fails without good cause to appear for the purpose of disputing the plaintiff’s claim against the defenders on whose behalf the summon was issued, or his own liability to the defendant…” (emphasis added.)

ከሚለው የእንግሊዘኛ ግልባጭ ጋር አያይዘን ከተመለከትነው ሦስተኛው ወገን ተከሳሽ በክርክሩ ውስጥ እንዲገባ ከተፈቀደ የክርክሩ ተካፋይ ሆኖ የሚያቀርበው ክርክር ሁለት ፈርጅ ሊይዝ የሚችል መሆኑን የሚያሣይ ነው፡፡ ይኸውም፤

  • 1ኛው ከተከሳሽ ጋር ሆኖ ድርሻ ክፍያ ወይም ስለተከሣሽ ሆኖ የካሣ ክፍያ የመክፈል ግዴታ ያለበት መሆኑን ተቀብሎ በተከሳሽ እግር በመተካት ተከሳሽ ለከሳሽ ኃላፊነት የማይኖርበት መሆኑን፤ ኃላፊነት አለበት ንኳ ቢባል ሊከፈል በሚገባው የካሣ መጠን ላይ ከከሳሽ ጋር ክርክር በማድረግ መሟገት የሚችልበት ክርክር ሲሆን
  • ሁለተኛው ደግሞ ድርሻ ወይም ካሣ ለመክፈል ለተከሳሽ ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ግዴታ የለብኝም በማለት መከራከር የሚችልበት መንገድ ነው፡፡

ስለሆነም የድንጋጌው ይዘት ብቻ ስንመለከተው እንኳ በክርክር ውስጥ ገብቶ እንዲከራከር የተጠራ ሦስተኛ ወገን ተከሣሽ በክርክሩ ከገባ በኋላ መሟገት የሚችለው ከተከሳሽ ጋር እንጂ ከከሣሽ ጋር ለመከራክር የሚያስችለው መብት የለውም የሚለው መደምደሚያ ህጋዊ ድጋፍ ያለው ሆኖ አላገኘነውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 23692 ቅጽ 6፣[1] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 43፣ 76፣ ፍ/ብ/ህ/ቁ 1908፣ 1909

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 43 መሰረት ወደ ክርክሩ እንዲገባ የሚጠራ ጣልቃ ገብ ተከራካሪ ወገን ከመነሻውም ከተከሳሹ ጋር የሕግ ወይም የውል ግንኙነት የለኝም በማለት ክርክር ከአቀረበ የክርክሩ ተሳታፊ የሚሆንበት አግባብ የለም፡፡ እንዲህ አይነት ክርክር እልባት ማግኘት ያለበት በተለየ ክስ እና የክርክር መዝገብ እንጂ ከሳሽ ባቀረበው መዝገብ ሊሆን አይገባም፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 43 ድንጋጌ አላማም እንዲህ አይነት ክርክሮችን ሁሉ በአንድ አይነት መዝገብ አጠቃልሎ ለመወሰን ነው ተብሎ አይታሰብም፡፡ ይልቁንም ጣልቃ ገብ ከመነሻውም ክዶ በተከራከረበት ጉዳይ የተከሳሽንና የጣልቃ ገብን ክርክርና ማስረጃ ሰምቶ ውሳኔ መስጠት ከሳሽ ያቀረበው ክስ ያላግባብ ጊዜና ወጪን እንዲጨምር የማድረግ ውጤት የሚኖረው ይሆናል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 79465 ቅጽ 14፣[2] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 43

በግጭት ምክንያት በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ መኪና ባለቤት ካሳ እንዲከፍል ክስ በቀረበበት ጊዜ መኪናው በመሸጡ ገዢው ወደ ክርክሩ እንዲገባለት ከጠየቀ የባለቤትነት ስሙ ወደ ገዢው ባይዘወርም ግጭቱ በደረሰበት ጊዜ ገዢው መኪናውን ተረክቦ በይዞታ ሥር ከነበረ ገዢው ወደ ክርክሩ መግባት አለበት፡፡ የመኪናው ባለቤትም ሆነ ጉዳቱ በደረሰ ጊዜ መኪናውን ሲጠቀምበት የነበረ ሰው ሁለቱም ኃላፉነት ቢኖርባቸውም የመጨረሻው የመካስ ኃላፊነት የሚወድቀው መኪናውን ይዞ ሲገለገልበት የነበረው ሰው ላይ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 41544 ቅጽ 8[3]

የዳኝነት ስልጣን

አንድን ክርክር በማስተናገድ ላይ ያለ የክልል ፍ/ቤት በፌዴራል መንግስት የተመዘገበ ተቋም (ድርጅት) አግባብነት ያለው የጣልቃ ገብ አቤቱታ በቀረበለት ጊዜ ጉዳዩን ጣልቃ ገቡን ወደ ክርክሩ በማስገባት አይቶ ለመወሰን ስልጣን የሌለው በመሆኑ ክርክሩ ጣልቃ ገብን ባካተተ መልኩ ለማየት ወደሚችለውና ስልጣን ላለው ፍ/ቤት ጉዳዩ ቀርቦ ሊታይ የሚገባ መሆኑን ገልጾ መዝገቡን መዝጋትና ተከራካሪዎችን ማሰናበት ይገባዋል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 90920 ቅጽ 15፣[4] ኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 80(4)፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ህገ መንግስት አንቀጽ 64(4)፣ ፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 9፣ 231(1) ለ፣ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁ. 25/1998 አንቀጽ 5(6)፣ 14

ይሁን እንጂ በአንድ ክርክር ሂደት ወደ ክርክሩ እንዲገባ የተደረገ ተከራካሪ ወገን ጉዳዩን የፌዴራል የሚያደርገው የነበረ ሁኖ እያለ ክሱን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት ስልጣን ሳይኖረው ስረ ነገሩን አስተናግዶ ዳኝነት ከሰጠ በኋላ ይኼው ተከራካሪ ወገን በይግባኝ ደረጃ በነበረው ክርክር የተሠጠውን ዳኝነት ተቀብሎ ከወጣ በኋላ በሌሎች ጉዳዩን የፌዴራል ሊያደርጉ በማይችሉ ተከራካሪ ወገኞች መካከል የተሰጠው ውሳኔ ከመነሻውም የፌዴራል ጉዳይ ነው ብሎ መወሰን አግባብነት የለውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 95033 ቅጽ 16፣[5] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 43(1)

 

[1] አመልካች አዋሽ ኢንሹራንስ ኩባንያ እና መልስ ሰጭዎች እነ አሊ መሐመድ ሐምሌ 03 ቀን 1999 ዓ.ም.

[2] አመልካች ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ/ማ እና ተጠሪ እነ አቶ አገኘው ገረመው /2 ሰዎች/ ጥር 14 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም.

[3] አመልካች ሠላም የሕዝብ ማመለለሻ አ/ማ እና ተጠሪ ኒያላ ኢንሹራንስ አ/ማ ሀምሌ 8 ቀን 2001 ዓ.ም.

[4] አመልካች ዓባይ ኢንሹራንስ አ.ማ እና ተጠሪዎች አቶ አለማየሁ አሰፋ ህዳር 06 ቀን 2006 ዓ.ም.

[5] አመልካች አቶ ስንታየሁ ተፈሪ እና ተጠሪ ወ/ሮ ማርታ በቀለ መጋቢት 25ቀን 2006 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (ከፊል የህግ አውጭነት) ስልጣን ምንነት፣ ባህርይ እና አስፈላጊነት

$
0
0

ምንነት እና ባህርይ

የአስተዳደር መ/ቤቶች ከመደበኛው የማስፈጸም ስልጣናቸው በተጨማሪ በህግ አውጭው በሚሰጣቸው ውክልና መሰረት አስተዳደራዊ መመሪያ የማውጣት ስልጣን አላቸው፡፡ የሚኒስትሮች ም/ቤት እንዲሁ ከተወካዮች ም/ቤት በሚሰጠው የውክልና ስልጣን ደንቦችን ይደነግጋል፡፡ ብቁና ውጤታማ አስተዳደር እንዲሰፍን የአስተዳደር መ/ቤቶች በህግ የተሰጣቸውን ስልጣን፣ ተግባርና ግዴታ በተጨባጭ ማሳካት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ስኬት እንዲኖር ደግሞ የማስፈፀም ስልጣን ብቻውን አይበቃም፡፡ ጠቅለል ያለ ይዘት ያላቸው በፓርላማ የሚወጡ ህጐች የፖሊሲ ደንቦችን ከማስቀመጥ ባለፈ ቴክኒካልና ዝርዝር ጉዳዮችን ስለማይዳስሱ በየጊዜው ለሚነሱ ችግሮች በዓይነትና በጥራት ምላሽ መስጠት ይሳናቸዋል፡፡ ስለሆነም በውክልና አስተዳደራዊ ድንጋጌዎችን የማውጣት ስልጣን አስፈላጊነት ከሁለት አቅጣጫዎች ማለትም ከአስተዳደር ስራ ውጤታማነት እና ከህግ አውጭው ውስንነት አንፃር ሊቃኝ ይችላል፡፡

አስተዳደራዊ ደንብና መመሪያ ማውጣት የአስተዳደር ህግ አይነተኛ መገለጫ ነው፡፡ ከነፃ ገበያ መከሰት በኃላ ተከትሎ የመጣው ዘመናዊው የማህበራዊ ዋስትና መንግስት (welfare state) ካስመዘገባቸው እድገቶች አንዱ የስራ አስፈፃሚው አካል ህግ የማውጣት ስልጣን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱ ነው፡፡

በውክልና ህግ ለማውጣት ዋናው የስልጣን ምንጭ ህግ አውጭው እንደመሆኑ የተወካዮች ም/ቤት በማያወላውልና ግልጽ በሆነ መልኩ ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ ለሚኒስትሮች ም/ቤት ወይም ለአስተዳደር መ/ቤቶች ካልሰጠ እነዚህ አካላት ደንብ ሆነ መመሪያ ለማውጣት ከህገ መንግስት የመነጨ ስልጣን የላቸውም፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የሚኒስትሮች ም/ቤት ሆነ የአስተዳደር መ/ቤቶች ደንብና መመሪያ እንዲያወጡ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ስልጣን አይሰጣቸውም፡፡ በፌደራል ደረጃ ህግ የማውጣት ስልጣን የተወካዮች ም/ቤት ሲሆን በክልል ደረጃ ደግሞ የየክልሉ ምክር ቤት ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ህግ የማውጣት ስልጣን የተሰጠው አካል በህገ-መንግስቱ ላይ የለም፡፡

ደንብና መመሪያ የማውጣት ስልጣን ምንጩ የተወካዮች ም/ቤት ብቻ ነው ከተባለ ይህ አካል ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ በውክልና ማስተላለፍ ይችላል? የሚለውን ጥያቄ መመርመሩ ተገቢ ሆናል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ላይ የተወካዮች ም/ቤት ህግ የማውጣት ስልጣኑን በውክልና እንዲያስተላልፍ የሚፈቅድለት ግልጽ ድንጋጌ የለም፡፡ ብዙዎች የመስኩ ምሁራን እንደሚስማሙበት ግን ህግ አውጭው ስልጣኑን በከፊል በውክልና ለማስተላለፍ ከህግ አውጭነቱ የሚመነጭ ስልጣን (inherent power) አለው፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን ያለገደብ ከህዝብ የተሰጠውን ስልጣን በውክልና ስም ሊያስተላልፍ አይችልም፡፡

በመሰረቱ በውክልና ስልጣን የሚወጣ ህግ ከመንግስት አስተዳደር እየተለጠጠ መምጣት ጋር ተያያዥ የሆኑ አስገዳጅ ሁኔታዎች ያመጡት ክስተት ነው፡፡ ስለሆነም እንደ ልዩ ሁኔታ እንጂ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት የለውም፡፡ ህግ አውጭው ምንም እንኳን በከፊል ስልጣኑን ማስተላለፍ ቢኖርበትም የፖሊሲ ጥያቄዎችን የሚነኩ መሰረታዊ ጉዳዩች በደንብ ወይም በመመሪያ እንዲወሰኑ ውክልና መስጠት የለበትም፡፡ የተፈጻሚነቱ ወሰኑ በህግ አውጪው በሚወጣው ህግ ላይ የሚታዩ ቀዳዳዎችን ለመድፈን ብሎም የፖሊሲ ጥያቄዎችን በማይነኩ ዝርዝርና ጥቃቅን ቴክኒካል ጉዳዮች መገደብ አለበት፡፡ ከዚህ አንጻር አፈጻጸሙ በጠባቡ ሊሆን ይገባዋል፡፡

        አስፈላጊነት

በተለያዩ አገራት እንደታየው ህግ አውጭው ከሚያወጣቸው ህጐች በበለጠ የአስተዳደር መ/ቤቶች የሚያወጧቸው መመሪያዎች እየበዙ መጥተዋል፡፡ በየጊዜው እያደገና እየተወሳሰበ የመጣው የመንግስት አስተዳደር ስራና የህግ አውጭው ለዚህ ስራ ውጤታማነት የሚያግዙ ህጐችን በዓይነትና በጥራት ለማቅረብ አለመቻል በውክልና ስልጣን የሚወጣ ህግ አማራጭ ሳይሆን የግድ መሆኑን ያሳየናል፡፡

አስፈላጊነቱ ጎልቶ ቢታይም በመስኩ ሊቃውንት ጠንካራ ተቃውሞ ሳይገጥመው አልቀረም፡፡ እንደብዙዎች እምነት የአስተዳደር መ/ቤቶች ህግ የማውጣት ስልጣን በዜጐች መብት ላይ በሩን ዘግቶ ለአምባገነናዊነት በሩን የሚከፍት አደገኛ አካሄድ ነው፡፡ የተቃውሞው መሰረቱ ንድፈ ሀሳባዊ ሲሆን የስልጣን ኢ-ተወካይነት ንድፈ ሀሳብ (theory of non delegability of power) አንዱ ነው፡፡ በላቲን (potestas delegari non potest delegare) ተብሎ ሲጠራ በእንግሲዝኛው (power once delegated should not be re-delegated) የሚል መልእክት አለው፡፡ ይህም ወደ አማርኛ ሲመለስ በውክልና የተሰጠ ስልጣን እንደገና በውክልና ሊተላለፍ አይችልም እንደ ማለት ነው፡፡ በአጭር አገላለፅ ህግ አውጭው ህግ የማውጣት ስልጣኑን የሚያገኘው ከመራጩ ህዝብ እንደመሆኑ ይህን በአደራ የተቀበለውን ስልጣን እንደገና (በድጋሚ) ለአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና ማስተላለፍ የለበትም ማለት ነው፡፡

የህግ አውጭነት የስልጣን ምንጩ ህዝብ ነው፡፡ የአንድ አገር ህዝብ ተወካዮቹን ሲመርጥ ችሎታና ብቃታቸውን መሰረት አድርጐ ያስተዳድሩኛል፤ ለእኔ ይሰሩልኛል፣ ትክክለኛውን ህግ ያወጡልኛል በሚል እምነት ጥሎባቸው ነው፡፡ ህግ አውጭው በውክልና በአደራ ከህዝቡ የተሰጠውን ስልጣን በአግባቡ በመገልገል ልማት፤ እድገት፤ ፍትህ፣ መልካም ስርዓትና ሰላም የሚያሰፍኑ ህጐችን ማውጣት አለበት፡፡ ህዝቡ ድምፁን ሰጥቶ ተወካዮቹን ሲመርጥና ስልጣን ሲሰጥ ይህን የህግ አውጭነት ስልጣን ላልተመረጡ ግን ለተሾሙ ስራ አስፈፃሚዎች በውክልና እንዲያስተላልፉት አይደለም፡፡ ከዚህ ሀሳብ በተቃራኒ ስልጣን በውክልና ከተላለፈ ህዝቡ ድምፅ ሰጥቶ ባልመረጣቸው (ስራ አስፈፃሚዎች) እየተገዛ ነው፡፡

ሁለተኛው የውክልና ህግ ንድፈ ሀሳባዊ ተቃውሞ ከስልጣን ክፍፍል መርህ (separation of powers) የሚነሳ ሲሆን ዞሮ ዞሮ መሰረቱ ለአምባገነናዊነት ያጋልጣል የሚል ነው፡፡ በስልጣን ክፍፍል መርህ መሰረት ህግ ማውጣት ለህግ አውጭው፤ ህግ መተርጐም ለፍርድ ሰጭው፤ ህግ ማስፈፀም ለአስፈጻሚ ተብሎ የእያንዳንዱ የመንግስት አካል ስልጣኑ ተመድቦና ተለይቶ ተሰጥቷል፡፡ አንድ የመንግስት አካል በተደራራቢነት ከአንድ በላይ ስልጣን የያዘ እንደሆነ ከራሱ በላይ ተቆጣጣሪ የሌለው ስልጣኑን በዘፈቀደ የሚጠቀም አምባገነን ይሆናል፡፡ ስለሆነም ስራ አስፈፃሚው ከተመደበለት ህግ የማስፈፀም ተግባር በተጨማሪ በደንብና መመሪያ ስም ህግ የሚያወጣ ከሆነ ሁለት የመንግስት ስልጣናትን ደርቦ ስለመያዙ ያም የስልጣን ክፍፍል መርህን መጣሱ ግልጽነቱ ጐልቶ የሚታይ ሀቅ ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሱት ሁለት ንድፈ ሀሳብ ተቃውሞዎች መሰረት በውክልና የሚወጣ ህግ አስተዳደራዊ አምባገነናዊነት፤ የበዘፈቀደ አሰራር እና በስልጣን አለአግባብ መገልገል እንዲስፋፋና ስር እንዲሰድ ያደርጋል በሚል ከመስኩ ባለሙያዎች የሰላ ሂስና ትችት ሲገጥመው ቆይቷል፡፡ ለምሳሌ እንግሊዝ አገር ውስጥ ሎርድ ሄዋርት የተባሉ የተከበሩ ዳኛና ምሁር በአገራቸው በየጊዜው በፍጥነት እያደገ የመጣውን የአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና ህግ የማውጣት ስልጣንና አሰራር The New Despotism በሚለው መጽሀፋቸው እ.ኤ.አ. በ1931 ዓ.ም. ያቀረቡት ጠንካራ ተቃውሞ የእንግሊዝ ፓርላማ ስለጉዳዩ የሚያጠና አጣሪ እንዲሾምና ውሳኔ እንዲያሳልፍ ምክንያት ሆኗል፡፡ ይሁን እንጂ ከምርመራው በኋላ የኬሪ ሪፖርት ተብሎ የሚታወቀው የምርመራ ሪፖርት የደረሰበት ድምዳሜ የውክልና ህግ እንግሊዝ ውስጥ በፍጥነት እያደገ መሆኑን ይህም በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ ተቀባይነት እንደሌለው ካተተ በኋላ በተግባር ግን የግድ አስፈላጊና መቅረት የሌለበት አሰራር መሆኑን በአጽንኦት ገልጿል፡፡

ስለሆነም ከላይ የቀረቡት ንድፍ ንድፈ ሀሳባዊ ተቃውሞዎች አሳማኝ የመሆናቸውን ያህል እየተወሳሰበ ከመጣው የመንግስት አስተዳደር ስራ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ተግባራዊ ምክንያቶች አስፈላጊነቱን አይቀሬና የበለጠ አሳማኝ አድርገውታል፡፡ የአስተዳደር መ/ቤቶች በህግ አውጭው በሚወጡት አዋጆች ላይ ብቻ ተንተርሰው ውጤታማ አስተዳደር ማስፈን አይቻላቸውም፡፡ ማህበራዊ አገልግሎት ለማቅረብ ሆነ መሰረተ ልማት ለመገንባት በአጠቃላይ በቅርበት ለሚታዩና በየጊዜው ተለዋዋጭ ለሆኑ ችግሮች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ቢያንስ የተወሰኑ ጉዳዮች ለአስተዳደር መ/ቤቶች ሊተዉ ይገባል፡፡ ለዚህም ይመስላል ታዋቂው የአስተዳደር ህግ ምሁር ዌድ (H.W.R. wade) የውክልና ህግን “መጥፎ ግን አስፈላጊ” (Necessary evil) ሲል የሚገልፀው፡፡ የውክልና ህግን በተግባር አስፈላጊ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የሚከተሉት በዋነኛነት ይጠቀሳሉ፡፡

ሀ. የጊዜ እጥረት

ህግ አውጭው ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ በውክልና ለማስተላፍ ከሚገደድባቸው ምክንያቶች አንዱ ከራሱ ከህግ አውጭነቱ የሚመነጭ ችግር ነው፡፡ አንድን አዋጅ ለመደንገግ ከሚወስደው ረጅም ጊዜና ተፈፃሚ ከሚሆነው የጠበቀ የስነ-ስርዓት አካሄድ አንፃር ውስብስብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚችሉ ህጐችን በብዛትና በጥራት ለማውጣት አስቸጋሪ ነው፡፡ የተወካዮች ም/ቤትን ያየን እንደሆነ ለሁለት ወራት የክረምት የእረፍት ጊዜና በመካከል ለአንድ ወር ለእረፍት ከተበተነ ጠቅላላ የስራ ጊዜው ከዘጠኝ ወራት አይበልጥም፡፡ ከዘጠኙ ወራት ውስጥ ቅዳሜና እሁድ ተቀንሰው በሚቀሩት የስራ ቀናት ባሉት አጭር የስራ ሰዓታት ለአገሪቱ አስፈላጊ አዋጆችን ከደቂቅ እስከ ልሂቅ ማውጣት አዳጋች ነው፡፡ የመስኩ ባለሞያዎች እንደሚናገሩት የአንድ አገር ፓርላማ ለተከታታይ 365 ቀናት፣ ድፍን 24 ሰዓታት በስራ ላይ ቢቆይ እንኳን በብዛትና በጥራት ለአገሪቱ አስፈላጊ የሆኑ ህጐችን ማቅረብ ይሳነዋል፡፡

ለ. የእውቀት እጥረት

የህዝብ ተመራጮች ለመመረጣቸው ምክንያት እውቀት ወይም ብቃት አንዱ መለኪያ ቢሆንም ዋናው መስፈርት ግን በህዝብ ዘንድ ያላቸው አመኔታና ተቀባይነት ነው፡፡ በጠቅላላ ጉዳዮች ጠቅላላ እውቀት ይኖራቸዋል ብለን ብንገምት እንኳን ከመንግስት አስተዳደር ውስብስብነት አንፃር ቴክኒካል በሆኑ ጉዳዮች ላይ የበለጠ እውቀትና ችሎታ ያለው በስራ አስፈፃሚው ዘንድ ነው፡፡ ስለሆነም ፓርላማው ትኩረቱን በፖሊሲ ጉዳዮች ላይ በማነጣጠር ዝርዝር የአፈፃፀም ስልት የሚጠይቁ ቴክኒካል ጉዳዮች በደንብና በመመሪያ እንዲወሰኑ ስልጣኑን በውክልና ማስተላለፍ የግድ ይለዋል፡፡ በፓርላማው ዘንድ የእውቀት እጥረት መኖሩ ብቻ ሳይሆን የአስተዳደር መ/ቤቶች በተቋቋሙለት ዓላማ ስር ልዩና ብቁ የሰው ኃይል ያላቸው መሆኑ ስልጣንን በውክልና ማስተላለፍ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ተመራጭም ያደርገዋል፡፡

ሐ. ተለዋዋጭ ሁኔታ

አንድ ህግ ፀድቆ ከወጣ በኃላ ወደፊት ለሚያጋጥሙ ችግሮች በሙሉ በቂ ምላሽ አይሰጥም፡፡ መሰረታዊው ችግር እልባት ቢያገኝ እንኳን ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚፈጠሩ የአፈፃፀም ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ የህግ አውጭው የህግ አወጣጥ ስነ-ስርዓት የጠበቀና ጊዜ የሚፈጅ ከመሆኑ አንፃር በየጊዜው የሚፈጠሩ ችግሮችን ከተለዋዋጭ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁኔታዎች አንጻር በተከታታይ አዋጅ በማውጣት ምላሽ መስጠት አይታሰብም፡፡ በተቃራኒው ደንብና መመሪያ የማውጣት ስነ-ስርዓት እጅጉን የቀለለ እንደመሆኑ ችግሮችን እየተከታተሉ አግባብነት ያለው መፍትሔ ለመስጠት ያስችላል፡፡ በውክልና ህግ የማውጣት ስልጣን ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ተለዋዋጭ መፍትሔ ለመስጠት አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

መ. አስቸኳይ ሁኔታ

አስቸኳይ መፍትሄ የሚሻ ጉዳይ ባጋጠመ ጊዜ አዋጅ ለማውጣት ከሚያስፈልገው ረጅም ጊዜ አንፃር ፈጣን ምላሽ መስጠት አስቸጋሪ ነው፡፡ በአንፃሩ ደንብና መመሪያ በአንድ ሳምንት ምናልባትም ከዚያም ባነሰ ጊዜ ሊወጣ ይችላል፡፡ ስለሆነም ልዩና አስቸኳይ እርምጃ ለመውሰድ አስፈላጊ በሆነበት ሁኔታ ከፓርላማው ይልቅ ስራ አስፈፃፀሚው ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ በውክልና ህግ የማውጣት ስልጣን አስፈላጊ ነው፡፡

 


Filed under: Articles

ማመሳሰል/መለየት እና የህግ ትርጉም አስገዳጅነት

$
0
0

አዋጅ ቁ. 454/1997 በስር ፍ/ቤቶች ላይ ድርብ ግዴታዎችን ይጥላል፡፡ የመጀመሪያው አግባብነት ባላቸው ሁኔታዎች የሰበር ችሎትን የህግ ትርጉም መቀበልና ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን የዚሁ ግዴታ ግልባጭ ገፅታ የሆነው ሁለተኛ ደግሞ አግባብነት በሌላቸው ሁኔታዎች ተፈጻሚ ከማድረግ መቆጠብ ናቸው፡፡ ለግዴታዎቹ ውጤታማነት ፈቃድ ብቻ ሳይሆን እውቀት ጭምር ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም በየትኛውም እርከን የሚገኝ ፍርድ ቤት በበፊተኛው የማመሳሰል በኋለኛው የመለየት ክህሎት ሊኖረው ይገባል፡፡

የሰበር ችሎት ትርጉም በሁሉም እርከን ላይ በሚገኙ ፍ/ቤቶች አስገዳጅነት እንዲኖረው ህግ አውጪው በአዋጅ ቁ. 454/1997 ሲደነግግ የአስገዳጅነት የተፈጻሚነት ወሰኑ በምን ዓይነት ጉዳዮች ላይ ሊሆን እንደሚገባ ብዙም አላስጨነቀውም፡፡ እናም እንደዋዛ በዝምታ አልፎታል፡፡ ይህን ችግር ችሎቱ አስቀድሞ የተገነዘበው ይመስላል፡፡ ጠቅለል ባለ አነጋገር ቢሆንም በአስገዳጅነት እና በጉዳዮች ዓይነት መካከል ያለውን ዝምድና በሰ/መ/ቁ. 61221 ቅጽ 14[1] ለመለየት ተሞክሯል፡፡

በአዋጅ ቁጥር 454/1997 አንቀጽ 2(1) ስር እንደተመለከተው ከአምስት ያላነሱ የዚህ ችሎት ዳኞች ተሰይመው የሚሰጡት የሕግ ትርጉም ተመሳሳይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በማናቸውም እርከን የሚገኝን ፍርድ ቤትን የሚያስገድድ ነው፡፡ አንድ የሕግ ትርጉም ለተመሳሳይ ጉዳይ ገዥነት እንዲኖረው ለማድረግ ደግሞ በመሰረታዊ ነጥቦች ላይ ጉዳዮቹ መመሳሰል ያለባቸው ስለመሆኑ ከአስገዳጅ የሕግ ትርጉም ፅንሰ ሀሳብ የምንገነዘበው ነው፡፡

የትኞቹ ናቸው መሰረታዊ ነጥቦች የሚባሉት? የተሟላ ባይሆንም ለጥያቄው በሰ/መ/ቁ. 67924 ቅጽ 13[2] ምላሽ ቀርቧል፡፡ በዚሁ መሰረት፤

በሀገሪቱ ወጥ የሆነ የህግ አተረጓጎምና አፈጻጸም ማስፈን ይቻል ዘንድ እንደ አንድ ስልት ተቆጥሮ በወጣው በአዋጅ ቁጥር 454/97 ድንጋጌ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች ተሰይመው የሰጡት የህግ ትርጉም በበታች ፍ/ቤቶች የአስገዳጅነት ኃይል ወይም ባህርይ የሚኖረው ትርጉም በተሰጠበት እና ዳኝነት እንዲሰጥበት [በቀረቡት] ጉዳዮች መካከል የተነሳው የፍሬ ነገርና የህግ ጥያቄ የተመሳሰለ ሆኖ ከተገኘ ብቻ ነው፡፡

እርግጥ ነው፤ ህግና ፍሬ ነገር መመሳሰል አለባቸው፡፡ ፈታኙ ጥያቄ ምን ያህል መመሳሰል አለባቸው ነው፡፡ ሙሉ በሚሉ መመሳሰል አለባቸው ወይስ በአብዛኛው መመሳሰል አለባቸው? በአብዛኛው ከተባለስ መመሳሰሉ ሊኖር የሚገባው ለህግ ትርጉም ቀጥተኛ ተዛምዶ ያላቸው ጥቂት ግን ደግሞ መሰረታዊ ፍሬ ነገሮች መመሳሰል ነው ወይስ በቁጥር የሚበዙት ፍሬ ነገሮች መመሳሰል?

ለእነዚህ ጥያቄዎች እጥር ምጥን ያለ ምላሽ ማስቀመጥ ይከብዳል፡፡ ከማመሳሰል ጋር የተያያዙ ተያያዥ ጥያቄዎች የብዙ ዘመናት የዳበረ ልምድ ባላቸው የኮመን ሎው አገራት ሳይቀር በአንድ ቀመር አልተፈቱም፡፡ እያንዳንዱ ክርክር የግል ባህርያት አሉት፡፡ ተመሳሳይ ጉዳዮችን በተመሳሳይ መንገድ የመወሰን ስርዓት ከዓላማው አንጻር (ወጥነትና ተገማችነት) ብቻ እየተመነዘረ ከታየ የሚያስጎመጅ ገጽታ ቢላበስም አደጋዎችም እንዳሉት መዘንጋት የለበትም፡፡ ይሄን ጠቃሚ ነጥብ የሰበር ችሎት ሳይቀር አምኖ ተቀብሎታል፡፡

እንደሚታወቀው ክርክሮች የሚወሰኑት እንደ የግል ባህሪያቸው እየታየ ነው፡፡ በአንድ ጉዳይ የተነሣውን ክርክር እልባት ለመስጠት የተሰጠ ውሣኔ በሌላ ጉዳይ ለተነሣው ክርክርም እልባት ለመስጠት ያስችላል ብሎ ሙሉ በሙሉ መደምደም ትክክልም ተገቢም አይይደም፡፡[3]

በችሎቱ የ10 ዓመት ጉዞ በበርካታ ውሳኔዎች የተሰጡ የህግ ትርጉሞች በስር ፍ/ቤት በቀዳሚነት ብሎም በደጋፊነት እየተጠቀሱ አከራካሪ የህግ ጭብጦችን ለመፍታት የማይናቅ ፋይዳ ማበርከታቸው ባይካድም ተጨማሪ የክርክር ምንጭ እየሆኑ መምጣታቸውም በገሀድ የሚታይ ሐቅ ነው፡፡ በታተሙት 19 ቅጾች ውስጥ የስር ፍ/ቤት ለውሳኔው መሰረት ያደረገው የሰበር መዝገብ ከተያዘው ጉዳይ ጋር አግባብነት የለውም ተብሎ በችሎቱ የተተቸበት አጋጣሚ በየጊዜው መጨመር እንጂ መቀነስ አላሳየም፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አግባብነት ያለው የህግ ትርጉም ሳይጠቀስ በዝምታ ታልፎ የሚሰጥ ውሳኔ ሰበር ደርሶ የሚታረምበት ክስተት ተደጋግሞ ታይቷል፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ በአዋጅ ቁ. 454/1997 በቸልታ የታለፈው የጉዳዮች መመሳሰል አሁን አሁን ትኩረት የሚያሻው ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የሰበር ችሎት ህግ በመተርጎም ብቻ ሳይሆን የራሱን ውሳኔዎች በመተርጎም ስራ መጠመዱ አይቀሬ ነው፡፡

የስር ፍ/ቤቶች በጥረትና በጥናት የታገዘ ልምድ እያካበቱ ሲመጡ የማመሳሰል ብቃታቸው በጊዜ ሂደት መዳበሩ አይቀርም፡፡ ሆኖም ማመሳሰል በቅንነትና በታማኝነት ካልታገዘ ውጤታማነቱ ይኮላሻል፡፡ ዳኞች ዳኝነት በሚሰጡበት መዝገብ ላይ ያሉትን ፍሬ ነገሮችና የህግ ነጥቦች ተመሳሳይ ይዘት ካለው የሰበር ውሳኔ ጋር በማነጻጸር የልዩነት ነጥቦችን ለማግዘፍ፤ የማይቀራረቡትን ደግሞ እንደምንም አጠጋግቶ ለማመሳሰል ሰፊ ስልጣን አላቸው፡፡ ከዚህ አድራጎት የሚገድባቸው ለዳኝነታዊ ስነ ምግባራቸው ያላቸው ተገዢነት ብቻ ነው፡፡ ዳኞች መሰረታዊ የህግ ስህተት የሚሰሩት ባለማወቅ ብቻ አይደለም፡፡ ከፊሎቹ በፍርድ ቤት የሚፈጸሙ ስህተቶች አንደኛውን ተከራካሪ ወገን ለመጥቀም ሆነ ተብሎ በማወቅ የሚሰሩ ስህተቶች ናቸው፡፡ እንዲህ ዓይነት ስህተቶች ሰበር ችሎት ብቻውን አያቃናቸውም፡፡ ልክ እንደ ህግ መተርጎም ሁሉ ማመሳሰልም ነጻ፣ ፍትሐዊና ገለልተኛ የዳኝነት ስርዓት ካልሰፈነ አያብብም፡፡ ይልቅስ በአጭር ይቀጫል፡፡

እዚህ ላይ የሰበር ችሎቱን ሚና ማውሳት ያስፈልጋል፡፡ ግልፅና ጥራት ያለው ውሳኔ ከሌለ ማመሳሰልን ይበልጥ አዳጋች ያደርገዋል፡፡ በስር ፍ/ቤቶች የተረጋገጡ ፍሬ ነገሮች አገላለጽ፣ መሰረታዊ የፍሬ ነገር እና የህግ ጥያቄዎችን በአግባቡ መለየት፣ ህጉ የተተረጎመበትን መንገድ ሳያወሳስቡ ማመልከት፣ መሰረታዊ የህግ ጥያቄው በየትኛው የህግ አተረጓጎም ስልት እንደተፈታ ማብራራት፣ የቋንቋውን የሰዋሰው ስርዓት የጠበቀ ቀላልና ሁሉም የሚረዳው አገላለጽ መጠቀም፣ አስገዳጅ የሆነውን ገዢ ደንብ (የህግ ትርጉም) አሳጥሮ ማጠቃለል በአጠቃላይ ለውሳኔው ይዘት ብቻ ሳይሆን ለውሳኔ አጻጻፍ መርሆዎችና ደንቦች ተገቢውን ቦታ መስጠት ወዘተ…ሁልጊዜ ከችሎቱ የሚጠበቁ ናቸው፡፡

ሰበር ችሎት የህግ ትርጉም ሰጠ ማለት የተተረጎመው ድንጋጌ አከራካሪነቱ ይቀራል ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም በችሎቱ ትርጉም ላይ የአረዳድ ልዩነት ይፈጠራል፡፡ ለዚህም ነው ችሎቱ በሰ/መ/ቁ. 80350 ቅጽ 14[4] የጥንቃቄ መልዕክት ለማስተላለፍ የተገደደው፤

ይሁን እንጂ ይህ የሰበር ሰሚ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም መንፈሱ በጥንቃቄ ታይቶ ግንዛቤ ካልተወሰደበት ከሕጉ ዓላማና መንፈስ ጋር የማይሄድ ውጤትን ማስከተሉ የማይቀር መሆኑ እሙን ነው፡፡

 

[1] አመልካች አቶ አከለ ምህረቱ እና ተጠሪ ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ መስከረም 22 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም.

[2] አመልካች ወ/ሮ ምንያ ገ/ሥስሴ እና ተጠሪዎች ወ/ሪት መሠረት ዓለማሁ መጋቢት 26 ቀን 2004 ዓ.ም.

[3] ሰ/መ/ቁ. 41535 ቅጽ 12 አመልካች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ተጠሪዎች እነ ግሎሪ ኃላፊነቱ/የተ/የግል ማህበር /4 ሰዎች/ ጥቅምት 3 ቀን 2003 ዓ.ም.

[4] አመልካች ሸራተን አዲስ እና ተጠሪ እነ አቶ ገናናው ከበደ /51 ሰዎች/ ጥቅምት 20 ቀን 2005 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

‘አሠሪና ሠራተኛ ሕግ’አዲስ መጽሐፍ

$
0
0

‘አሠሪና ሠራተኛ ሕግ’ በገበያ ላይ ውሏል፡፡ በዩኒቨርሳል የመጽሐፍት መደብር (አራት ኪሎ)ያገኙታል፡፡

ማውጫ        DOWNLOAD

የሰበር ውሳኔዎች ማውጫ    DOWNLOAD

የሕግጋት ማውጫ        DOWNLOAD

ዋቢ መጻህፍትና ጽሑፎች   DOWNLOAD

የቃላት ማውጫ             DOWNLOAD

 

 

የተመረጡ ገጾች                              

ዝውውር እና የአሠሪው ስልጣን፡ የሰበር አቋም ሲፈተሽ     DOWNLOAD

የኃይማኖት ተቋም ሠራተኞች                         DOWNLOAD

በጥፋት ምክንያት ሠራተኛን ስለማሰናበት         DOWNLOAD

የሥራ መደብ መሰረዝ                          DOWNLOAD


Filed under: Articles, Case Comment, Employment law, Labour Conventions

Consolidated Ethiopian Laws 1934-2017 (Vol. I-IV)

Consolidated Ethiopian Laws 1934-2017 (Vol. V-VII)

Links to Law Journals in Ethiopia

oromiya jsptlri modules

‘ሰድቦ ለሰዳቢ’፡ በፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የፀያፍ ቃላት አገላለጽ

$
0
0

በእኛ አገር ‘ተሰደብኩኝ ስሜ ጠፋ’ ብሎ ለፖሊስ የሚያመለክት ሰው አንድም አልታደለም አሊያም አዙሮ አላሰበም፡፡ ወደ ፖሊስ ያመራው በሰው ፊት ሲሰደብ፣ ስሙ ሲጠፋ መጠቃቱ አንገብግቦት፣ በንዴት ሰክሮ ባስ ሲልም ራሱን መቆጣጣር አቅቶት ይሆናል፡፡ ክብሩ ተነክቷልና ይሄ ጥጋበኛ ሰዳቢ በፍትሕ ፊት ቀርቦ የእጁን ማግኘት አለበት፡፡ ተሰደብኩኝ ባይ ወደ ፖሊስ በማምራት አንዴ የጠፋ ስሙን ለማደስ ባይችልም በእርግጥም ፍትሕ ያገኝ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን ከሚያገኘው ይልቅ የሚያጣው ነገር ይበልጣል፡፡

በመጀመሪያ ‘እከሌ እንዲህ ብሎ ሰደበኝ’ የሚል ማመልከቻ ይዞ ፖሊስ ጣቢያ ሲሄድ ይህ ማመልከቻው በትንሹ በ3 እና 4 ፖሊስ እይታ ውስጥ ይገባል፡፡ ስድቡ ለጆሮ የሚዘገንን ወይም ቃላቶቹና አገላለጻቸው በአካባቢው ከተለመደው የተለየና ወጣ ያለ ከሆነ መርማሪው ፖሊስ እንዲሁም ማመልከቻውን ያነበቡ ፖሊሶች ወሬውን በጨዋታ መልክ ለሌሎች ፖሊሶች ሹክ ማለታቸው አይቀርም፡፡ አስቂኝ ይዘት ካለው ደግሞ የወሬ ቅብብሎሹ እስከ ዕለቱ ተረኛ ፖሊሶች ድረስ ይዛመታል፡፡

ቀጥሎ ባለው ሂደት ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ይከፍትና ማመልከቻውም ከግላዊ ወደ መንግስታዊ ሰነድነት ይሸጋገራል፡፡ አመልካች በለስ ቀንቶት ከጊዜ በኋላ ሹመት ቢያገኝ፣ ዝና ቢቀዳጅ ፖሊስ የእርሱን ማመልካቻ አውጥቶ አይቀደውም፡፡ መዝገቡን ለአዲሱ ስሙ ሲል አያጠፋውም፡፡ በቃ! ሁሌ እዛው ነው፡፡

በምርመራ መዝገቡ ውስጥ የአመልካች ቃል እና የምስክሮች ቃል ይሰፍራል፡፡ የምስክሮችን ብዛት በትንሹ በሁለት ብንወስነው አመልካችን ያንገበገበው የስድብ ቃል ሶስት ጊዜ ይደገማል፤ አንዴ ራሱ የከሳሽነት ቃል ሲሰጥ፣ ሁለቴ ምስክሮች ቃላቸውን ሲሰጡ፡፡ ቃሉ በተጠራ ቁጥር በከፊልም ቢሆን አመልካች መሸማቀቁ አይቀርለትም፡፡ ባይሸማቀቅ እንኳን ጥጋበኛውን ሰዳቢ እያስታወሰ በውስጡ ይበግናል፡፡

በምርመራ ሂደት ተጠርጣሪው እንዲቀርብ በተበዳይ በኩል መጥሪያ ይላክለታል፡፡ መጥሪያ ሲቀበል ብቻውን አይሆንም፡፡ ጓደኛቹ፣ የሥራ ባልደረቦቹ፣ ጎረቤቶቹ ይኖራሉ፡፡ የፖሊስ ጣቢያ ማህተም ያረፈበት ሰነድ ሲያዩ ስለጉዳዩ ይጠይቁታል፡፡ በድንገተኛ አጋጣሚ በተፈጠረ አለመግባባት ወይም ጥል እንደሰደበው ይነግራቸዋል፡፡ ወይም አመልካች ራሱ ቀድሞ ስለሰደበው እርሱም በተራው እንደሰደበው ይነግራቸዋል፡፡ መቼም ‘ምን ብለህ ሰደብከው?’ ብለው መጠየቃቸው አይቀርም፡፡ በዚህ መልኩ የአመልካችን መሰደብ በትንሹ ተጨማሪ 3 ሰዎች ሰሙ ማለት ነው፡፡

ተጠርጣው ፖሊስ ጣቢያ ሲቀርብ በቀላሉ ወደ ቤቱ አይመለስም፡፡ ማረፊያ ቤት ይገባል፡፡ በነጋታው ወይም ከሁለት ቀናት በኋላ ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡ መርማሪ ፖሊስ እንደለመደው ምርመራዬን አላጠናቀቅኩም ብሎ የጊዜ ቀጠሮ ይጠይቅበታል፡፡

ተጠርጣሪው በጊዜ ቀጠሮ ሲቀርብ ‘እከሌን እንዲህ ብሎ ስለሰደበው’ ተብሎ ቁጥር በያዘ የፍርድ ቤት መዝገብ ላይ ይመዘገባል፡፡ ይህ መዝገብ እንደ ምርመራው መዝገብ ሁሉ ለብዙ ዓመታት የአመልካችን የመሰደብ ታሪክ የሚናገር መንግስታዊ ሰነድ ሆኖ ይቆያል፡፡ ተጠርጣሪው ጥፋቱን በወ/መ/ስ/ስ/ህግ ቁ. 35 መሰረት ካመነ ይህም በመዝገቡ ላይ ይሰፍራል፡፡ ዳኛው ይሰሙታል፡፡ ሬጅስትራር እና ፋይል ከፋች ምናልባትም ችሎት ጸሐፊ እየተቀባበሉ ያነቡታል፡፡ በፖሊስ ጣቢያ ቆይተው የጊዜ ቀጠሮ የሚጠባበቁ ተጠርጣሪዎችም ዜናው ይደርሳቸዋል፡፡ መቼም ‘ምን አጥፍተህ ገባህ?’ እያለ መጠየቃቸው፣ ሌሊቱን ማውጋታቸው አይቀርም፡፡ አመልካች ራሱ ‘እከሌ እንዲህ ብሎ ሰደበኝ’ ብሎ በማመልከቻው ላይ እንደወረደ ያሰፈረው ጸያፍ የስድብ ቃል በዚህ መልኩ በፍጥነት ይዛመታል፡፡

በመጨረሻም የምርመራ መዝገቡ ተጠናቆ ለዓቃቤ ህግ ሲላክ ቢያንስ 5 ዓቃቤ ህጎች (በ1 ለ5 ተጣምረው) የአመልካችን መሰደብ ያውቃሉ፡፡ ከተጠርጣሪው አፍ የወጣው ጸያፍ ቃል ሳቅ የሚያጭር ከሆነ በር ዘግተው በሳቅ ፍርስ ይላሉ፡፡ የግል ገጠመኛቸውን እያነሱ በጉደኛው መዝገብ ይዝናናሉ፡፡

በመጨረሻም በሰነድ እና በሰው በፍጥነት የተሰራጨውና (ምናልባትም የድራፍትና የቡና ማጣጫ የሆነው) ጸያፍ ቃል በዐቃቤ ህግ ክስ ላይ እንደወረደ ተጽፎ ለመደበኛ ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡ ክሱን ሬጅስትራርና ዳኛው ያነቡታል፡፡ ከሁሉ የከፋው ደግሞ ምስክሮች በችሎት ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ሲናገሩት ታዳሚው ሁሉ ይሰማዋል፡፡ ለዛውም በተደጋጋሚ፡፡ በዋና ጥያቄ ተከሳሽ የግል ተበዳይን ምን እንዳለው? ዓቃቤ ህግ ይጠይቃል፣ በመስቀለኛ ጥያቄ ‘አንተ እንዲህ ስለው ሰምተሃል?’ ሲል ተከሳሽ ይጠይቃል፡፡ ዳኛውም በማጣሪያ ጥያቄ ‘ተከሳሹ የግል ተበዳይን በትክክል ምንድነው ያለው?’ ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ምስክሩ ለእያንዳንዱ ጠያቂ ምላሽ ሲሰጥ ቃሉን ከአንድ ጊዜ በላይ ይጠራዋል፡፡ ተከሳሽ ሸረኛ ከሆነ ደግሞ በመስቀለኛ ጥያቄ ሰበብ ‘እኔ ተከሳሹን እንዲህ ብየዋለው?’ ‘እሺ እንዲህ ስለው አንተ የት ነበርክ?’ ‘እንዲህ ብዬ የሰደብኩት ጮክ ብዬ ነው?’…እያለ የግል ተበዳይን በድጋሚ ሊያሳርረው ይችላል፡፡

የግራ ቀኙ ማስረጃና ክርክር ተመርመሮ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሲሰጥ የጸያፍ ቃሉ መዛመት ያበቃለታል ተብሎ ይገመታል፡፡ እውነታው ግን ከግምቱ የተለየ ነው፡፡ ጸያፍ ቃሉ በውሳኔውም ላይ ፈጦ ይታያል፡፡ ከተከሳሽ አፍ የወጣው ለጆሮ የሚዘገንን ቃል በሚዘገንን መልኩ የውሳኔው አካል ይሆናል፡፡ ለዛውም እየተደጋገመ፡፡ ከሳሽ ዓቃቤ ያቀረበው ክስ ሲገለጽ፣ የዓቃቤ ህግ ምስክሮች ቃል ሲዘገብ፣ ፍርድ ቤቱ ምክንያት ሲሰጥ፣ ድምዳሜ ላይ ሲደርስ ቃሉ በጥሬው ይደጋገማል፡፡

በግምት ከሁለት ወራት በፊት ዓቃቤ ህግ የመንግስትን ክብር አንቋሸሸ ባለው ግለሰብ ላይ ያቀረበው ለየት ያለ ክስ በማህበራዊ ድረ-ገጽ ላይ ተለቆ ነበር፡፡ ይኸው ግለሰብ መንግስትን “ቡሽቲ ነው፡፡” እንዳለና ሌሎች ቅስም ሰባሪ አስጸያፊ ቃላትን እንደተናገረ በክሱ ዝርዝር ላይ ተጠቅሷል፡፡ የክሱ መቅረብ ከተከሳሽ አፍ የወጡትን አጸያፈ ቃላት አሉታዊ ውጤት አጋነነው እንጂ አልቀነሰውም፡፡

እስካሁን የቀረበው ሀተታ ዓላማ በስድብ፣ ስም ማጥፋት፣ ዛቻ፣ አስነዋሪና አጸያፊ ቃላትና ድርጊት ክብራቸው ተነክቶ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች በደላቸውን በገሀድ እንዳያሰሙ አሊያም ፍትህ እንዳይሹ ተስፋ ማስቆጥ አይደለም፡፡ በወንጀል ጉዳይ ዝምታ መምረጥ ወንጀልን የሚያባብስ እንደመሆኑ መፍትሔ ማግኘቱ ግድ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነት የወንጀል ክስ አቤቱታዎች ከፖሊስ ጣቢያ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ የሚስተናገዱበት ስርዓት የተበዳዩን ግላዊ ሁኔታ ለአደባባይ በማያጋልጥ መልኩ በተለየ መንገድ መከናወን ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይም አስጸያፊና አስነዋሪ ቃላት እና ተግባራት በፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የሚሰፍሩበትና የሚገለጹበት መንገድ ከተበዳይ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከውሳኔ አሰጣጥ መርሆች አንጻር ትኩረት የሚያስፈልገው አነጋጋሪ ርዕስ ነው፡፡

እውነትነቱን ማረጋገጥ ባልችልም አንድ ወዳጄ እንዳጫወተኝ በድሮ ጊዜ አጸያፊ ቃላት በፍርድ ላይ በጥቅል ገላጭ መጠሪያ ነበር የሚገለጹት፡፡ ለምሳሌ በተለምዶ የሚታወቁ ክብር የሚነኩ አስጸያፊ ቃላት ‘ቅስም ሰባሪ’ በሚል ይመደባሉ፡፡ ስለሆነም ተከሳሹ ተበዳዩን እንዲህ ብሎ ስለደበው በማለት ቃሉን በመጠቀም ፈንታ ‘ቅስም ሰባሪ ስድብ ስለሰደበው’ የሚል አገላለጽ በውሳኔው ላይ ይሰፍራል፡፡ ከአባላዘር በሽታ፣ ከወሲብ እና ሐፍረተ ስጋ ጋር በተያያዘ ክብረ ነክ የሆኑ አጸያፊ ቃላት ደግሞ ‘ጋብቻ ከልክል’ በሚል ይፈረጃሉ፡፡

እነዚህ የአገላለጽ መንገዶች በእርግጥ ፍርድ ቤቶች ሲጠቀሙባቸው እንደነበረ ማረጋገጫ ባይኖርም በአሁኑ ወቅት የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ ‘እያቆሸሹ’ የሚገኙት አጸያፊ ቃላት ግን ዘዴ ተፈልጎላቸው ተጠራርገው ሊወጡ ይገባል፡፡ ፍርድ በባህርዩ በተከራካሪዎች መካከል መብትና ግዴታ ከመፍጠር የዘለለ ውጤት አለው፡፡ እንዲያውም ይህን ግላዊ ሚናውን ከተወጣ በኋላ በዘላቂነት የሚቆየው መገለጫው ህዝባዊ ሰነድነቱ ነው፡፡ ፍርዱን ተማሪዎች ያነቡታል፤ መምህራን ይመረምሩታል፣ ተመራማሪዎች በጥልቀት ይተነትኑታል፡፡ ከዚያም አልፎ ፍላጎት ያለው የማህበረሰብ ክፍል ለተለያየ ምክንያት ያነበዋል፡፡

ከአስፈላጊነት አንጻር ካየነው የእነዚህ ቃላት መገለጽ በተከራካሪዎች መብትና ግዴታ ብሎም በፍርዱ ይዘት ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ ከተከሳሹ አፍ የወጣው ቃል በዐቃቤ ህግ ክስ ላይ እስከተጠቀሰ ድረስ ፍርድ ቤቱ ‘ተከሳሽ ተበዳይን በዐቃቤ ህግ ክስ ላይ የሰፈረውን ቃል በመናገር እንደሰደበው’ በፍርዱ ላይ ጠቋሚ መግለጫ ከሰጠ የተከራካሪዎችን የይግባኝ መብት አያጣብብም፡፡

አጸያፊ ቃላት በመገኛኛ ብዙኃን በቀጥታ አይነገሩም፡፡ እነዚህ ተቋማት ምንም እንኳን እውነትን ሳያድበሰብሱ ለታዳሚያቸው የማቅረብ ግዴታ ቢኖርባቸውም ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ጸያፍ ቃላትን ቆርጠው ያስቀራሉ፡፡ ህዝብ ፊት የሚቀርብ የሚዲያ ውጤት የቱንም ያክል ቀዳሚ ዓላማው እውነትን ሳይጨምር ሳይቀንስ ለታዳሚው ማስተላለፍ ቢሆንም ጸያፍ ቃላት ለጆሮ ያልተገቡ፣ ሰቅጥጭ ነውራዊ ስሜት የሚፈጥሩ በመሆናቸው መቅረታቸው ግድ ነው፡፡ ይህ መሆኑ የሚዲያ ውጤቱ የተከበረ ያደርገዋል፡፡ በተጨማሪ የአገር ባለጌ የተናገረውን ሁሉ እንደወረደ መዘገብ ባለጌዎችን የማበረታታት ያክል ነው፡፡

እንደ ሚዲያ ውጤት ሁሉ ፍርድ ቤትም ውሳኔው ‘የተከበረ’ ሊሆን ይገባል፡፡

በተግባር እንደምናየው አብዛኛዎቹ ፍርድ ቤቶች ለስድብ እና መሰል ወንጀሎች ከሚሰጡት አነስተኛ ቦታ የተነሳ ብዙውን ጊዜ ሰዳቢ (ተከሳሽ) አንድም ቅጣቱ ተገድቦለት ወደ ቤቱ እያፏጨ ይሄዳል፡፡ አሊያም እዚህ ግባ በማይባል የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ሆኖም ለክሱ ምክንያት የሆነው ስድብና አጸያፊ ቃል እስከመጨረሻው የፍርዱ አካል ሆኖ ይቀራል፡፡ የግል ተበዳይ ላይ ያልተለጠፈበት ስድብ አሁን ፍርዱ ላይ ይለጠፋል፡፡ እና ማነው የግል ተበዳይን የበለጠ የጎዳው? የሰደበው ተከሳሽ ወይስ ለሰዳቢ ያጋለጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ?


Filed under: Articles

የዕድሜ ልክ እስራት 25 ዓመት ነው?

$
0
0

አንዳንዴ እንደ ቀላል የሚወሰዱ የህግ ጉዳዮች የክርክር ምንጭ ይሆናሉ፡፡ የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ትርጓሜን በተመለከተ ከአንድ በላይ የህግ ባለሞያ ጋር ክርክር ገጥሜ አውቃለው፡፡ ጭብጡ ይህን ይመስላል? ‘የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ቅጣት የተፈረደበት ሰው ማረሚያ ቤት ታስሮ የሚቆየው ለ25 ዓመታት ነው? ወይስ ዕድሜ ልኩን ማለትም እዛው ማረሚያ ቤት ውስጥ እስኪሞት ድረስ?’

በወንጀል ህጉ ላይ ነጻነትን የሚያሳጡ አራት ዓይነት ቅጣቶቸ ተቀመጠዋል፡፡ እነሱም፤

ቀላል እስራት ከ10 ቀን እስከ 3 ዓመት በልዩ ሁኔታ እስከ 5 ዓመት /አንቀጽ 106/

ጽኑ እስራት

  • ከአንድ ዓመት እስከ 25 ዓመት አንቀጽ /አንቀጽ 108(1)/
  • በህግ በግልፅ በተደነገገ ጊዜ ዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት /አንቀጽ 108(1)/

የሞት ቅጣት

የሞት ቅጣት ሲወሰን ህጉ የሚከተሉት ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ ያስገድዳል፡፡

  • ወንጀሉ እጅግ ከባድ ወንጀለኛውም በተለይ አደገኛ ሲሆን
  • ለወንጀሉ ቅጣት እንዲሆን በህጉ በግልጽ ከተደነገገ
  • ወንጀለኛው ቅጣት ማቅለያ የሌለው ሲሆን
  • ዕድሜው ከአስራ ስምንት ዓመት በላይ ሲሆን
  • ወንጀሉ ፍጻሜ ያገኘ ሲሆን

የወ/ህ/ቁ. 108/1/ ከአንድ እስከ ሃያ አምስት ዓመት የሚያስቀጣውን መደበኛውን ጽኑ እስራት  ከዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት በግልጽ ይለያል፡፡ ድንጋጌው የጽኑ እሥራት ቅጣት ግቡ ተቀጪው እንዲታረምና ወደ ማህበራዊ ኑሮ እንዲመለስ ከማድረግ በተጨማሪ በተለይ ለኀብረተሰቡ ደህንነት በጥብቅ ቁጥጥር ሥር እንዲቆይ ለማድረግ እንደሆነ ከደነገገ በኋላ የጽኑ እስራት ቅጣት ጊዜው ከአንድ ዓመት እስከ ሃያ አምስት ዓመት እንደሚደርስ ሆኖም በሕጉ ተገልጾ የተደነገገ ሲሆን ጽኑ እስራት እስከ ዕድሜ ልክ እንደሚዘልቅ ይናገራል፡፡ በግልጽ አማርኛ ስናስቀምጠው የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት የተወሰነበት ሰው ዕድሜ ልኩን እስኪሞት ድረስ በእስር ይቆያል፡፡

የህጉ መልዕክት አሻሚነት ባይኖረውም የዕድሜ ልክ እስራትን በ25 ዓመት የሚገድቡ አስተያየቶች ከህግ ባለሞያው ዘንድ ሲሰነዘር ይታያል፡፡ የወንጀል ህጉ መግቢያ ሳይቀር ተመሳሳይ የተዛባ ሀሳብ ይንጸባረቅበታል፡፡ በመግቢያው ላይ የሚከተለው ዓረፍተ ነገር ሰፍሮ ይገኛል፡፡

በተወሰኑ ወንጀሎች ረገድ የእስራት ወይም የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ቢሆንም ዋናው አስተሳሰብ ጥፋተኞቹ ለጊዜው ወይም ለዘለቄታው በኀብረተሰቡ ላይ ተጨማሪ ወንጀል እንዳይፈጽሙበት ለመከልከል ነው፡፡ እንዲህ በሆነ ጊዜም ከሞት ቅጣት በቀር የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው ጥፋተኞች እንኳ ቅጣታቸውን ሳይጨርሱ በአመክሮ ሊለቀቁ ይችላሉ፡፡

ቅጣታቸውን ሳይጨርሱ? ዕድሜ ልክ የተፈረደበት ሰው ከፊቱ የሚጠብቀው ዕለተ ሞቱን ነው፡፡ እናም የሚጨርሰው ቅጣት የለም፡፡ ዕድሜ ልክ አያልቅም፡፡ ስለሆነም በመግቢያው ላይ የሰፈረው ዓረፍተ ነገር ጣዕም ያለው ይዘት የሚኖረው ቅጣታቸውን ሳይጨርሱ የሚለው ሐረግ ተቆረጦ ሲወጣ ነው፡፡

የዕድሜ ልክ እስራትን ከ25 ዓመት ጽኑ እስራት ጋር በማቀላቀል የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ባብዛኛው ምንጫቸው በአመክሮ መፈታትን የሚመለከቱት ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ በዚህ ረገድ አግባብነት ያለው ድንጋጌ የወንጀል ህጉ ቁ. 202 ሲሆን ሙሉ ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

አንቀጽ ፪፻፪ ለመለቀቅ የሚያበቁ ሁኔታዎች 

፩  ተቀጪው ከተወሰነበት የእሥራት ጊዜ ከሦስት  እጅ ሁለቱን እጅ ወይም ፍርዱ የዕድሜ ልክ እሥራት ሲሆን ሃያ ዓመት በፈፀመ ጊዜ አግባብ ባለው አካል ወይም በጥፋተኛው አሳሳቢነት ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛው በአመክሮ እንዲፈታ መወሰን የሚችለው ጥፋተኛው፡-

ሀ/ አስፈላጊ የሆነውን ነፃነት የሚያሳጣ ቅጣት ወይም የጥንቃቄ እርምጃ በመፈፀም ላይ ሳለ በሥራውና በጠባዩ የተረጋገጠ መሻሻል አሳይቶ እንደሆነ፣

ለ/ ለደረሰው ጉዳት በተቻለ መጠን ሊከፍል የሚጠበቅበትን በፍርድ ቤት በተወሰነው መሠረት ወይም ከተበዳዩ ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት ካሣ ለመክፈሉ ማረጋገጫ አቅርቦ እንደሆነ፣ እና

ሐ/ አመሉና ጠባዩ በመልካም አኗኗር ለመኖር የሚያስችለው እና በአመክሮ መፈታቱ መልካም ውጤት ሊያስገኝ ይችላል ተብሎ የታመነ እንደሆነ፣ ነው፡፡

ከድንጋጌው ምንባብ እንደምንረዳው የዕድሜ ልክ እስራት የተወሰነበት ሰው ሃያ ዓመት ከታሰረ በኋላ በአመክሮ ሊፈታ ይችላል፡፡ አመክሮ በልዩ ሁኔታ የሚፈቀድ እንጂ መብት አይደለም፡፡ የወንጀል ህግ ቁ. 201 በደነገገው መርህ መሰረት ለአመክሮ በተወሰነ ገደብ መፈታት የተቀጪውን ጠባይ ማሻሻያና ወደ ደንበኛው ማህበራዊ ኑሮ መመለሻ ሆኖ ሊቆጠር ይገባዋል፡፡ ተቀጪው ለዚሁ ተገቢ ካልሆነና በተወሰነ ገደብ መፈታቱ ተፈላጊውን ውጤት የሚያስገኝ መሆኑ ካልታመነበት በቀር ሊፈቀድ አይቻልም፡፡ ህጉ ያስቀመጠው መርህ በተግባር እንዲረጋገጥ በቁ. 202 ላይ የተዘረዘሩት ሶስት ቅድመ ሁኔታዎች ሊሟሉ ይገባል፡፡

የተነሳንበትን ርዕስ ስናጠቃልል ዕድሜ ልክ የተፈረደበት ሰው በአመክሮ ሊፈታ የሚችልበት ዕድል መኖሩ የቅጣቱን ዓይነት መሰረታዊ ይዘት አይቀይረውም፡፡ መሰረታዊ ይዘቱ ተቀጪው ዕድሜ ልኩን እንደሚታሰር፣ ህይወቱን በሙሉ እስረኛ ሆኖ እንደሚቆይ ነው የሚያስገነዝበን፡፡ ህጉም የሚለው ይህንኑ ነው፡፡


Filed under: Articles

የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በክልሎች ላይ ያለው ስልጣን ህገ-መንግስታዊ ስላለመሆኑ –ክፍል ፩

$
0
0

በህዝብ እንባ ጠባቂ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 211/1992 አንቀጽ 4 መሰረት በፌደራሉ መንግስት የተቋቋመው ፌደራል እንባ ጠባቂ በክልል መንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላትና ባለስልጣናት የሚፈፀሙ የአስተዳደር ጥፋቶችን የመመርመር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 210/1992 አንቀጽ 4 አዋጁ በማንኛውም ክልል ውስጥ በሚፈፀሙ የሰብዓዊ መጣስ ጉዳዮችም ላይ ስልጣን እንደሚኖረው ይደነግጋል፡፡ የሁለቱም አዋጆች አንቀጽ 4 አፈላጊነት ሆነ ህገ-መንግስታዊነቱ በሚገባ የተመከረበትና የታሰበበት ካለመሆኑም በላይ በተግባር የክልሎችን የዲሞክራሲያዊ ተቋም ግንባታ ጅምሮ ከማዳከም በቀር ተጨባጭ ፍሬ አላስገኘም፡፡

የዚህ ጽሁፍ ዋና ዓላማ ተቋሙ ሆኖ ኮሚሽኑ በክልሎች ላይ የተሰጣቸው ስልጣን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት የማይፈቅደው ስለሆነም ህገ-መንግስታዊ መሰረት እንደሌለው ብሎም ከተግባራዊ ምክንያቶች አንጻር የማያስኬድና ለአፈፃፀም የማይመች ስለመሆኑ አሳማኝ መከራከሪያዎች ማቅረብ ነው፡፡

ቀጥሎ በሚቀርው ዳሰሳ ውስጥ በተለየ ሁኔታ ካልተመለከተ በስተቀር እንባ ጠባቂ የሚለው ቃል በተመሳሳይ መልኩ ኮሚሽኑንም ያጠቃልላል፡፡ በሁለቱም ማቋቋሚያ አዋጆች ላይ የሚገኙት ድንጋጌዎች ከይዘት አንጻር ብቻ ሳይሆን ከአንቀጽ አቀማመጥ ጀምሮ ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ በተጨማሪም ኮሚሽኑ ሆነ ተቋሙ ስያሜያቸው ቢለያይም በአሰራርም በተግባርም በስልጣንም /Power/ ሁለቱም ያው እንባ ጠባቂዎች ናቸው፡፡ በሁለቱ መካከል ያለው ቀጭን ልዩነት የስልጣን ክልል (jurisdiction) ልዩነት ነው፡፡ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የአስተዳደር ጥፋቶችን ኮሚሽኑ ደግሞ የሰብዓዊ መብት መጣስ ጉዳዮችን በተመለከተ የመመርመር የመከታተል፣ የመቆጣጠርና የመመርመር ስልጣን አላቸው፡፡ በሌላ አነጋገር ኮሚሽኑ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች እንባ ጠባቂ ሲሆን ተቋሙ ደግሞ የአስተዳደር ጥፋቶች እንባ ጠባቂ ተብሎ ሊፈረጅ ይችላል፡፡ በዚህ የተነሳ ከዚህ በታች የሚቀርቡት መከራከሪያዎች ላይ በጥቅሱ እንባ ጠባቂ የሚለው ቃል ለሁለቱም በወካይነት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በመከራከሪየነት የሚነሱት መሰረታዊ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡

  • እንባ ጠባቂ የማቋቋም ህገ-መንግስታዊ ግዴታ
  • ራስን በራስ የማስተዳደር መብት
  • እንባ ጠባቂ-እንደ ፓርላማ ክንፍ
  • የተቋሙ መፍትሔ ይዘትና አፈጻጸም
  • የአቅም ውስንነት
  • ለተቋሙና ተሿሚው ያለው ከበሬታ

እንባ ጠባቂ የማቋቋም ህገመንግስታዊ ግዴታ

እንባ ጠባቂ በክልል መንግስታት ላይ ስልጣን ሊኖረው ይገባል ወይስ አይገባም? የሚለው ጥያቄ ተቋሙን ሆነ ኮሚሽኑን በኢትዮጵያ ውስጥ በዝርዝር ህግ ለማቋቋም ከታሰበበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ገሃድ የወጣ ክርክርና ውይይት አልጋበዘም፡፡ በክልል መንግስታት ዘንድም ውስጥ ውስጡን የጉርምርምታ ምንጭ ቢሆንም ጉዳዩ በጭብጥነት ተመዞ የመነጋገሪያ አጀንዳ ለመሆን አልበቃም፡፡ ተቋሙንና ኮሚሽኑን ለማቋቋም በነበረው የህግ ማውጣት ሂደት እንደዚሁ ሁለቱም አካላት በክልሎች ላይ የሚኖራቸው ስልጣን ህገ-መንግስታዊነትና ተግባራዊነት በተመለከተ ህገ-መንግስቱን ተንተርሶ የተሰጠ ትንተና ሆነ ምክንያት አልነበረም፡፡

ከላይ እንደተጠቆመው የሁለቱም ተቋማት ማቋቋሚያ አዋጆች በክልል መንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላትና ባለስልጣናት የሚፈፀሙ የአስተዳደር ጥፋቶችና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተቋሙና በኮሚሽኑ የስልጣን ክልል ስር እንደሚወድቁ ደንግገዋል፡፡   በዚህ ረገድ የተፈጠረው የተሳሳተ ግንዛቤ ምንጩ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 55 ንኡስ አንቀፅ 14 እና 15 ንባብ ስለመሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ሁለቱም አንቀጾች የተወካዮች ምክር ቤት ስልጣንና ተግባር በሚዘረዝረው የህገ መንግስቱ አንቀፅ 55 ውስጥ የሚገኙ ሲሆን ምክር ቤቱ የሠብዓዊ መብት ኮሚሽንንና የእንባ ጠባቂ ተቋምን እንደሚያቋቁም ብሎም ስልጣንና ተግባራቸውን በህግ እንደሚወሰን በማያሻማ አነጋገር ይደነገጋሉ፡፡

የአንቀጽ 55/14/ እና /15/ ድንጋጌዎችን ላይ ላዩን ለሚያነብ ሰው ሁለቱም ተቋማት በፌደራል መንግስት ስልጣን ስር እንደሚካተቱ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ይችላል፡፡ የሁለቱም ተቋም ማቋቋሚያ አዋጆች በሚረቀቁበት ወቅት ተቋማቱን አስመልክቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቀረበ አንድ ሪፖርት ላይ ተቋማቱ በክልሎች ላይ ስልጣን ሊኖራቸው እንደሚገባ ለማሳመን የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 55 /14/እና /15/ ተጠቅሰዋል፡፡ ስለሆነም በዚህ ረገድ ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ማጥራት ያስፈልጋል፡፡

የእንባ ጠባቂ በየአገራቱ ዝብርቅርቅ መልክና ቅርጽ አለው፡፡ ሆኖም ከሚቋቋምበት መንገድ አንጻር ሲታይ በአንድ መንግስታዊ ተቋም ስር (ለምሳሌ የዩኒቨርስቲ[1] እና የማረሚያ ቤት እንባጠባቂ[2])፣ በግሉ ዘርፍ (ለምሳሌ የባንኮች፣ የኃይል አቅርቦት፣ የኢንሹራንስ፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እንባጠባቂዎች[3]) እንዲሁም በጣም በሚታወቅበት መልኩ በአገር አቀፍ፣ በክልሎች፣ ግዛቶችና መስተዳድሮች ደረጃ ይቋቋማል፡፡

በግሉ ዘርፍ እና በተቋም ደረጃ የሚገኘውን ትተን በአገር ዓቀፍ ደረጃ የሚቋቋመውን እንባ ጠባቂ በጥቅል ስንመለከት የሚቋቋምበት መንገድ ሁለት ነው፡፡ ይኸውም አንደኛ አገሪቱ ባጸደቀችው ህገ መንግስት በግልጽ ዕውቅና የተሰጠው ሊሆን ይችላል፡፡ ሁለተኛ በህገ መንግስት ላይ በግልጽ ሳይካተት ፓርላማ በሚያወጣው ልዩ ህግ ሊቋቋም ይችላል፡፡ የተቋሙ የህልውና መሰረት ህገ መንግስት መሆኑ/አለመሆኑ አንድ መሰረታዊ ቁምነ ነገር ያስጨብጠናል፡፡ ይኸውም ህገ መንግስታዊ ዕውቅና ያለው እንባ ጠባቂ ተቋም የመቋቋሙ ዕጣ ፈንታ ለህግ አውጪው የተተወ አይደለም፡፡ ህግ አውጪው መዋቅርና አደረጃጀቱን በልዩ ህግ በመወሰን ተቋሙን የመመስረት ህጋዊ ግዴታ አለበት፡፡ በተቃራኒው የአንድ አገር ህገ መንግስት ስለተቋሙ በግልጽ ካልደነገገ እንደ ህግ አውጪው ፈቃድ እንባ ጠባቂ ሊኖርም ላይኖርም ይችላል፡፡ ህልውና የሚያገኘው አስፈላጊነቱና ጠቃሚነቱ ከታመነበት ብቻ ነው፡፡

የእንባ ጠባቂ ጽንሰ ሀሳብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ከሞላ ጎደል በሁሉም የዓለማችንን አገራት ሰፊ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተቋሙ የመንግስትን ተጠያቂነት በማረጋገጥ ብሎም አስተዳደራዊ ፍትሕ በማስፈን ሊጫወት የሚችለው ዴሞክራሲያዊና ህገ መንግስታዊ ሚና መሰረታዊ ጥያቄ ባይነሳበትም የተወሰኑ አገራት እጃቸውን ዘርግተው አልተቀበሉትም፡፡ ሌሎች ደግሞ ትልቅ ቦታ ከመስጠታቸው የተነሳ ህልውናው በየምርጫ ዘመን በሚቀያየር ፓርላማ ላይ ጥገኛ እንዳይሆን በማሰብ ጠንካራ ህገ መንግስታዊ መሰረት እንዲኖረው አድርገውታል፡፡ የተቀሩት ደግሞ ህገ መንግታዊ ዕውቅና እስከ መስጠት ደረጃ ባይደርሱም በልዩ ህግ በማቋቋም ህልውና እና ዕውቅና ሰጥተውታል፡፡ ስለሆነም ሲፈለግ ይኖራል፤ ከገዜ በኋላ ካልተፈለገ ይቀራል፡፡

አልባኒያ the People’s Advocate በመባል የሚጠራውን እንባ ጠባቂ ተቋም እ.ኤ.አ በ1998 ዓ.ም. ባጸደቀችው ህገ መንግስት ላይ የማቋቋሚያውን መሰረት ከጣለች በኋላ በቀጣዩ ዓመት በይፋ ህግ እንዲቋቋም አድርጋለች፡፡[4] ሆኖም የኦስትሪያ እንባ ጠባቂ ቦርድ ህገ መንግስታዊ መሰረት ስላልነበረው ተቋሙን የማቋቋም ሀሳብ መጀመሪያ ተቀባይነት ሳያገኝ ከጊዜ በኋላ በህግ ሊቋቋም ችሏል፡፡ የህጉ ረቂቅ ለፓርላማ የቀረበው እ.ኤ.አ በ1972 ዓ.ም. ሲሆን ከሶስት ዓመታት በኋላ ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ሆኖም ከዚሁ ረቀቂ ይዘትና መንፈስ በመነሳት በድጋሚ የቀረበው ረቂቅ እ.ኤ.አ በ1977 ተቀባይነት አግኝቶ ቦርዱ ሊቋቋም ችሏል፡፡[5] በአሜሪካ የፌደራል እንባ ጠባቂ የሚባል ተቋም የለም፡፡ ኮንግረስ ስራ አስፈጻሚውን መቆጣጠር ለራሱ ብቻ የተተወ ህገ መንግስታዊ ሚና እንደሆነ ጠንካራ አቋም በመያዙ ይህን ታሪካዊ ስልጣኑን አሳልፎ መስጠት አልፈቀደም፡፡[6] የዚህ አመለካከት ተጽዕኖ ተቋሙ ከጥቂት ግዛቶች[7] በስተቀር በአብዛኞቹ ተቀባይነት እንዳያገኝ ምክንያት ሆኗል፡፡

ወደ አገራችን ስንመጣ ሁለቱም ተቋማት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 55/14/ እና /15/ ላይ መሰረታቸው ተጥሏል፡፡ የተወካዮች ምክር ቤት ስልጣንና ተግባራቸውን በዝርዝር ህግ ከመወሰን ውጪ አስፈላጊነታቸውን ጥያቄ የሚያነሳበት ጉዳይ አይደለም፡፡ ሁለቱም ድንጋጌዎች በግልጽ የሚናገሩት ምክር ቤቱ ተቋማቱ ህጋዊ ሰውነት አግኝተው ስራቸውን እንዲያከናውኑ የማድረግ ህገ መንግስታዊ ግዴታ እንዳለበት ነው፡፡ ይሄ ግዴታ በሌሎች ሶስት ህግ መንግስታዊ መሰረት ባላቸው ተቋማትም ላይ ተፈጻሚነት አለው፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ከአንቀጽ 111-113 ድረስ የተጠቀሱት የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት፣ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ እና የህዝብ ቆጠራ ኮሚሽን እንደ እንባ ጠባቂ ሁሉ ህገ መንግስታዊ ናቸው፡፡

የድንጋጌዎቹን ይዘት ከፌደራላዊ የስልጣን ክፍፍል ጋር ማምታታት የፌደራላዚም ስርዓት ሀሁ ግንዛቤ የማጣት ያክል ነው፡፡ የአንቀጽ 55 ርዕስ ‘ስልጣንና ተግባር’ ስለሚል ብቻ ሁለቱም ተቋማት በፌደራል መንግስት የስልጣን ክልል ስር እንደሆኑ ማሰብ ትርጉም አለመስጠቱ ብቻ ሳይሆን ፌደራሊዝምን በአሀዳዊነት መነጽር የማየት ችግር ያንጸባርቃል፡፡

ለመሆኑ ‘እንባ ጠባቂ ተቋም እና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በፌደራል መንግስት ስልጣን ስር ናቸው ማለት ምን ማለት ነው?’ በፌደራል እና ክልል ስልጣን (jurisdiction)[8] ስር የሚወድቁ ጉዳዮች በአንቀጽ 51 እና 52 ስር ተለይተው ተዘርዝረዋል፡፡ ዝርዝሮቹ በሙሉ የሚናገሩት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፍ ስር ስላሉ ጉዳዮች ነው፡፡ ስልጣን በፌደራል እና በክልል የሚከፋፈለው አንድ ተቋም በሚያከናውነው ጉዳይ እንጂ ተቋሙን ራሱን የፌደራል/የክልል በማለት አይደለም፡፡ ለዚህም ነው እንባ ጠባቂ የፌደራል ብቻ ነው የሚል አነጋገር ትርጉም የማይሰጠው፡፡

ህገ መንግስቱ የክልል መንግስታት የራሳቸውን እንባ ጠባቂና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እንደሚያቋቁሙ ሳይናገር በዝምታ ማለፉ ተገቢና ትክክል ነው፡፡ ምክንያቱም ውሳኔው ከመነሻው የክልሎቹ የራሳቸው ነው መሆን ያለበት፡፡ ሲፈልጉ በህገ መንግስታቸው ለተቋማቱ ዕውቅና መስጠት ይችላሉ፡፡ አሊያም ደግሞ በህገ መንግስታቸው ውስጥ ማካተቱን ትተው አስፈላጊ ሆኖ ባገኙት ጊዜ ህግ አውጥተው ማቋቋም (አሊያም እስከነጭራሹ አለማቋቋም) ይችላሉ፡፡

ሲጠቃለል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 55 /14/ እና /15/ ድንጋጌዎች ይዘት የፌደራሉ እንባ ጠባቂ ህገ መንግስታዊ እንደሆነና የተወካዮች ምክር ቤት በዝርዝር ህግ ስልጣንና ተግባሩን በመወሰን ህጋዊ ሰውነት ኖሮት እንዲቋቋም የማድረግ ህገ መንግስታዊ ግዴታ እንዳለበት ነው፡፡ ስለሆነም ሁለቱም ተቋማት በክልል መንግስታት ስራ አስፈጻሚ ላይ ስልጣን እንዳላቸው ከድንጋጌዎቹ በመነሳት የሚቀርብ ክርክር ፈር የሳተና የፌደራል ስርዓት ከሚያስነሳቸው ዘርፈ ብዙ ጭብጦች ውስጥ ሊካተት የማይችል፣ ጥልቀት ያነሰው፣ ‘ከላይ-በላይ ንባብ’ የሚመነጭ ክርክር ነው፡፡ ብዙ ባያስኬድም ከስልጣን ክፍፍል አንጻር ክርክር ከቀረበ መቅረብ ያለበት ተቋማቱ ከፌደራልና ከክልል በየትኛው ስልጣን ስር እንደሚወድቁ በመጠየቅ ሳይሆን ተቋማቱ የሚያከናውኑት ጉዳይ በማን ስልጣን ስር እንደሆነ ጥያቄ በማንሳት ነው፡፡ ስለሆነም ጥያቄው የሚከተለውን መልክ ይይዛል፡፡ ‘የክልል ስራ አስፈጻሚ አካላትንና ባለስልጣናትን ተጠያቂነት ማረጋገጥ፣ በክልሉ አስተዳደራዊ ፍትሕ ማስፈን፣ ለአስተዳደራዊ በደሎች መፍትሔ መስጠት፣ አስተዳደራዊ ጥፋትን የማረም ስልጣኑ የማን ነው? የራሱ የክልሉ ነው? ወይስ የፌደራል መንግስት? በክልል ጉዳይ የሚያገባው ማነው? የፌደራል ወይስ የክልሉ መንግስት?’

የጥያቄዎቹ ቀላልነት ሲታይ ምላሽ መስጠት መሰረታዊ ባልሆነ ጉዳይ መባከን ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ ከ500 በላይ አባላት ያቀፈ ፓርላማ ጥያቄውን በወጉ መመለስ ተስኖት ‘ፈተናውን የወደቀ’ እንደመሆኑ በቂ ማብራሪያ መስጠት ግድ ይላል፡፡

[1] ለበለጠ ግንዛቤ Mundinger, Donald C. 1967. “The University Ombudsman: His Place on the Campus.” The Journal of Higher Education (Ohio State University Press) 493-499. Accessed June 27, 2014. http://www.jstor.org/stable/1980338. ይመለከቷል፡፡

[2] ለበለጠ ግንዛቤ Fulmer, Richard H. 1981. “The Prison Ombudsman.” Social Service Review (The University of Chicago Press) 55: 300-313. Accessed June 27, 2014. http://www.jstor.org/stable/30011474. ይመለከቷል፡፡

[3] Trevor Buck, Richard Kirkham and Brian Thompson, The Ombudsman enterprise and administrative Justice. (ashgate publishing company፣ 2011) ገፅ 7

[4] Joachim Stern, Albania. In G. Kucsko-Stadlmayer (Ed.), European Ombudsman-Institutions A comparative legal analysis regarding the multifaceted realisation of an idea. (SpringerWienNewYork, 2008) ገፅ 70

[5] Brigitte Kofler, Austria. In G. Kucsko-Stadlmayer (Ed.), European Ombudsman-Institutions A comparative legal analysis regarding the multifaceted realisation of an idea. (SpringerWienNewYork, 2008) ገፅ 90

[6] Kass, Benny L. 1967. “We Can, Indeed, Fight City Hall: The Office and Concept of Ombudsman.” American Bar Association Journal (American Bar Association) 53 (3): 231-236. Accessed June 28, 2104. http://www.jstor.org/stable/25723944.

[7] ለምሳሌ ሀዋይ፣ ኔብራስካ፣ አዮዋ፣ አላስካና አሪዞና የእንባ ጠባቂ ተቋም በህግ አቋቁመዋል፡፡ Hill, Larry B. 2002. “The Ombudsman Revisited: Thirty Years of Hawaiian Experience.” Public Administration Review (Wiley/American Society for Public Administration) 61: 24-41. Accessed June 27, 2014. http://www.jstor.org/stable/3110280.

[8] ምንም እንኳን በኢ.ፌ.ዲሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 51 እና 52 የእንግሊዝኛ ቅጂ ርዕሶች ላይ ህግ አውጪው የተጠቀመው powers and duties የሚል ቢሆንም የስልጣን ክልልን ወይም ወሰንን በአግባቡ የሚገልጸው ቃል jurisdiction ነው፡፡


Filed under: Articles

የጠ/ሚኒስቴር ጽ/ቤት፡ የስልጣን ምንጭ እና ህጋዊነት

$
0
0

ከ10 ዓመት በላይ ማንሳትና መጣል በኋላ ‘የአስተዳደር ህግ መግቢያ’ የሚለው መጽሀፌ እነሆ 2010 ላይ ሲጠናቀቅ ትልቅ እፎይታ ተሰምቶኛል፡፡ የህትመት ነገር ከተሳካ በቅርቡ ገበያ ላይ ይውላል፡፡ የሚከተለው ጽሁፍ የተወሰደው ከመጽሐፉ ረቂቅ ላይ ነው፡፡

የጠ/ሚኒስቴር ጽ/ቤት፡ የስልጣን ምንጭ እና ህጋዊነት

በተለምዶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት (አንዳንዴ ቢሮ) እየተባለ የሚታወቀው አካል ስልጣንና ተግባሩ በህግ ተወስኖ አልተቋቋመም፡፡ በአቋሙ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግል ቢሮ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህገ መንግስቱ የተሰጡትን ስልጣንና ተግባራት በአግባቡ እንዲያከናውን ለማገዝ የሚረዱ የቢሮ ስራዎችን ከማከናወን በስተቀር በማናቸውም መንግስታዊ ሆነ አስተዳደራዊ ጉዳዮች የመወሰን ሆነ ለበታች አካላት መመሪያ የማስተላለፍ ስልጣን የለውም፡፡

ጽ/ቤቱ በታሪካዊ አቋሙ ከነበረው የቆየ ስም እንዲሁም የደርግ መውደቅን ተከትሎ በሽግግሩ መንግስት ጊዜ በዘልማድ በሚያከናውናቸው መንግስታዊ ተግባራት (በተለይ ቅሬታ ሰሚ በመሆን) የተነሳ በህግ ሳይሆን በዕውቅና (de facto) ህልውና ያገኘ የመንግስት ተቋም ለመሆን በቅቷል፡፡

በሰ/መ/ቁ. 16195[1] ተጠሪዎች በመንግስት ለተወረሱ መኖሪያ ቤቶቻቸው አበል እንዲከፈላቸው የሥራና ከተማ ልማት ሚ/ር በወሰነላቸው መሰረት ይከፈላቸው ዘንድ በአመልካች ላይ ክስ አቀረቡ፡፡ ከክርክሩ በኋላ ክሱ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ያለው አበል እንዲከፈላቸው ተፈረደላቸው፡፡ ፍርዱም በከፍተኛው ፍ/ቤት ፀና፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎት ሻረው፡፡ በመዝገቡ ላይ የሥራና ከተማ ልማት ሚ/ር ውሳኔ በጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ እንደተሻረ ተመልክቷል፡፡ በዚህ መልክ መሻሩ ለስር ፍ/ቤቶችን ውሳኔ ለመሻር ምክንያት ሆኗል፡፡ ችሎቱ ህገ መንግስቱን በማጣቀስ ለማብራራት እንደሞከረው፤

[በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.] ህገ-መንግስት አንቀጽ 74/4/ ሁሉም ሚኒስቴሮች የሚገኙበትን የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚመራ፣ እንደሚያስተባብርና እንደሚወክል ተመልክቷል፡፡ እንዲሁም…የአስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አ/ቁ 4/87 አንቀጽ 11/1/ ሥር እያንዳንዱ ሚኒስትር፣ የሚመራውን ሚኒስቴር መ/ቤት የሚመለከቱ ሥራዎች ፕሮግራሞችና ህጎች አፈፃፀም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለሚኒስቴሮች ምክር ቤት መሆኑ ተገልጿል፡፡ ከነዚህ ህጎች አኳያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚኒስቴር መ/ቤቶችን በበላይነት የመምራትና ስራቸውንም የመቆጣጠር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴር መ/ቤቶቹ ሥራቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት የፈፀሙትን ስህተት ማረምና ማስተካከል በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን ስር የሚወድቅ ነው፡፡

የሥራና ከተማ ልማት ሚ/ር ውሳኔን የሻረው ጽ/ቤቱ እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አይደለም፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎት የውሳኔውን ህጋዊነት ያጣራው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ህገ መንግስታዊ ስልጣን በማመሳከር ነው፡፡ ሁለቱ እንደ አንድ አምሳል፣ አንድ አካል ተቆጥረዋል፡፡ ይህ የማደባላለቅ ስህተት በሌሎች የህግ ባለሞያዎች ላይም ይታይል፡፡ በቅርቡ የጠቅላይ ዓቃቤ ባጠናቀረው የተጠቃለሉ ህጎች ማውጫ ላይ ‘ለጠ/ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት ተጠሪ የሆኑ አስፈጻሚ አካላትን ማቋቋሚያ ህጎች’ የሚል ርዕስ እናገኛለን፡፡

ከላይ ለመጠቆም እንደተሞከረው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የሀገሪቱ ርዕሰ መስተዳድር የግል ቢሮ ነው፡፡ የግል የሆነበት ምክንያት እንደ አገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት በህግ አልተቋቋመም፡፡ የፕሬዚዳንቱ ጽ/ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 131/1991 ጽ/ቤቱን ህጋዊ ሰውነት አላብሶ አቋቁሞታል፡፡ ለጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ግን ተመሳሳይ የህግ መሰረት የለም፡፡ በስልጣኑ ላይ የሚነሳው ህጋዊና ህገ መንግስታዊ ጥያቄ የማቋቋሚያ አዋጅ አለመኖር ብቻ አይደለም፡፡ ከጊዜ በኋላ ጽ/ቤቱን የሚያቋቁም አዋጅ ቢወጣም እንኳን ከጽህፈት ስራ የዘለለ በማናቸውም መንግስታዊ ጉዳዮች ውሳኔ የማስተላለፍ ሚናና ተግባር ሊኖረው አይችልም፡፡

የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከህገ መንግስቱ የሚመነጩት ስልጣናት ከእርሱ በቀር ወደ ሌላ አይተላለፉም፡፡ ከምክትል ጠ/ሚኒስትሩ በቀር ሚስት/ባል፣ ልጅ፣ ወላጅ፣ ጽ/ቤት ሆነ ሌላ ማናቸውም አካል የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስልጣን መጋራት አልተፈቀደላቸውም፡፡ በህግ የተቋቋመ የሚኒስቴር መ/ቤት የሰጠውን ውሳኔ ጽ/ቤቱ መሻር ይችላል ማለት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጅ ተመሳሳይ የመሻር ስልጣን አለው የማለት ያክል ነው፡፡

የሰበር ችሎት ይህን ግዙፍ ህገ መንግስታዊ ስህተት በሰ/መ/ቁ. 34665[2] ላይም ደግሞታል፡፡ በመዝገቡ ላይ የተነሳው የህግ ጥያቄ የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት (ደብተር) የመሰረዝ ስልጣን ህጋዊነት ሲሆን የፍሬ ነገሩ መነሻ ታሪክ አስደማሚና አስገራሚ ነው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ በወቅቱ ማለትም በ1991 ዓ.ም. ላይ የስራና ከተማ ልማት ሚ/ር በመስሪያ ቤቱ ይገኙ የነበሩ የቤት ጉዳዮችን ከሰራተኞቹ ጋር ለአዲስ አበባ መስተዲድር ምክር ቤት ስራና ከተማ ልማት ቢሮ እንዲያስረክብ ከጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት ትእዛዝ ደረሰው፡፡ በትዕዛዙ መሰረት ሚኒስቴር መ/ቤቱ ጉዳዮቹንና ሰራተኞቹን አስረከበ፡፡ የአ/አበባ መስተዳድ ቤት ስራና ከተማ ልማት ቢሮ ከየካቲት 1 ቀን 1991 ዓ.ም ጀምሮ የቤት ጉዳዮቹን ተረክቦ ማስተዳደር ጀመረ፡፡ ቢሮው በዚህ ሁኔታ የአመልካቾችን ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር በመሰረዙ ምክንያት በስር ፍ/ቤት ክስ አቅርበው ጥያቄያቸው ተቀባይነት አጣ፡፡ ይግባኝ ቢሉም አቤቱታቸው ውደቅ በመደረጉ ጉዳዩ ወደ ሰበር ችሎት አመራ፡፡ አመልካቾች በሰበር ክርክራቸው ደብተሩ ስልጣን በሌለው አካል እንደተሰረዘ በመጥቀስ የቢሮውን ተግባር ህጋዊነት ሞግተዋል፡፡

በህግ የተቋቋ የመንግስት መ/ቤት ስልጣን፣ መብትና ግዴታ ወደ ሌላ የሚተላለፈው ህግ አውጭው አምኖበት በአዋጅ ሲያጸድቀው ብቻ ነው፡፡ አንድ መ/ቤት በበላይ ትዕዛዝ (ያውም በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት) የሚበተን ከሆነ፣ ስልጣኑን ተቀምቶ ወደ ሌላ የሚተላለፍ ከሆነ ያኔ ህጋዊነትና ስርዓት አልበኝነት አንድ ሆነው ተዋህደዋል፡፡ የሰበር ችሎት ይህ አስደንጋጭ እውነት  አልተገለጠለትም፡፡ የስር ፍ/ቤቶችን ውሳኔ ሲያጸና በሰ/መ/ቁ. 16195 ያሰፈረውን (የተሳሳተ) ትንተና በመድገም ነገሩን በአጭሩ ቋጭቶታል፡፡ በሰ/መ/ቁ. 34665 የተለየ ነጥብ የሚስተዋለው ጠቅላይ ሚኒስትሩና ጽ/ቤቱ ቦታ ተቀያይረዋል፡፡ ለንፅፅር ይረዳ ዘንድ ሙሉ ዓረፍተ ነገሩ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

የጠቅላይ ሚ/ጽ/ቤት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ስራ የመከታተልና በበላይነት የመቆጣጠር ስልጣን ያለው እንደመሆኑ መጠን የስራና ከተማ ልማት ሚ/ር ቤቶችን የሚመለከት ጉዳይ ለአ/አበባ ስራና ከተማ ልማት ቢሮ እንዲያስተላልፍ በተሰጠው ትእዛዝ መሰረት ስራውንና ሰራተኞቹን ለቢሮው አስተላልፏል፡፡ (ሰረዝ የተጨመረ)

 

[1] አመልካች የኪራይ ቤቶች ድርጅት እና ተጠሪ እነ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃ/ስላሴ /6 ሰዎች/ ቅጽ 4 ሚያዝያ 11 ቀን 1999 ዓ.ም.

[2] አመልካች እነ አቶ ናትናኤሌ ዘውገ /2 ሰዎች/ እና ተጠሪ እነ ወ/ሮ እግዜሩ ገ/ሕይወት /2 ሰዎች/ ሰ/መ/ቁ. 34665 ቅጽ 10 ጥቅምት 12 ቀን 2002 ዓ.ም


Filed under: Articles

የአስተዳደራዊ ድንጋጌዎች ህጋዊነትና ህገ መንግስታዊነት

$
0
0

ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ሲፈጠር መፍትሔ የመሻት ቀዳሚ ኃላፊነት የተጣለባቸው በየዘርፉ የተቋቋሙ የአስተዳደር መ/ቤቶች ናቸው፡፡ ከትምህርት አሰጣጥ ወይም ጋር ጥራት ጋር የተያያዘ ወይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ችግር ሲከሰት የትምህርት ሚኒስቴር እንቅስቃሴ ይጀምራል፡፡ በጉምሩክ ህግ አፈጻጸም አቤቱታዎች ሲጎርፉ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መፍትሔ ያፈላልጋል፡፡ በግንባታ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች ጉዳት ሲደርስባቸው የሠራተኛ ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ላይ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ትኩረት ሰጥቶ ስራ ይጀምራል፡፡ ችግሮችን ለመቅፍ መላ መዘየድ ችግር የለውም፤  እንዲያውም ይበረታታል፡፡

ይሁን እንጂ በአንድ አገር ውስጥ በየጊዜው የሚፈጠሩ ችግሮች ሊቀረፉ የሚገባው በህግና በህገ መንግስት ማዕቀፍ ውስጥ ነው፡፡ ከፊል ጉዳዮች የተወካዮች ም/ቤትን ጣልቃ ገብነት ይሻሉ፡፡ የአስተዳደር መ/ቤቶች ችግር ፈቺነት አቅም በህግ ከተፈቀደላቸው ስልጣን በላይ ሊለጠጥ አይችልም፡፡ አዋጅ ሊመልሰው የሚገባውን መመሪያ ከቀደመው መ/ቤቶች ችግር ፈቺ መሆናቸው ቀርቶ ችግር ፈጣሪ ይሆናሉ፡፡ የአስተዳደር ድንጋጌዎች መመዘኛ አስፈላጊነትና ጠቀሜታ ብቻ ሳይሆን በዋናነት ህጋዊነት ነው፡፡ የቄሳርን ለቄሳር እንዲሉ ተወካዮች ሊመክሩበትና ሊፈቱት የሚገባውን ችግር ተሿሚዎች በመመሪያ ለመቅረፍ መሽቀዳደም የለባቸውም፡፡ የሚከተለው አጭር ዳሰሳ መመሪያ እና ደንብ እያስከተሉት ያለውን የህጋዊነትና ህገ መንግስታዊነት አደጋ በአጭሩ ያስቃኛል፡፡

 1. የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአምልኮ ስርዓት

በትምህርት ተቋማት የአምልኮ ስርዓትን በሚመለከት የትምህርት ሚኒስቴር በ2000 ዓ.ም. መመሪያ አውጥቷል፡፡[1] መመሪያው ከመዋዕለ ህጻናት እስከ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች ድረስ በሁሉም የትምህርት ተቋማት ተፈጻሚ የሚሆነውን የአምልኮ፣ የአለባበስ እና የአመጋገብ ስርዓት ይደነግጋል፡፡ በአንቀጽ 6.2 እስከ 6.6 ድረስ ከተፈቀዱና ከተከለከሉ ተግባራት መካከል እንደ ቅደም ተከተሉ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡

  • 2 የተማሪ ደንብ ልብስ በማያስፈልጋቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሁኔታው በወርክሾፕ፣ በላቦራቶሪ፣ ወይም በህክምና ትምህርት ተቋማት ሙያው ወይም ስልጣናው የሚፈልገው አይነትና የአንዱን ወይም የሌላውን እምነት የማይጋፋ የአለባበስ ስርዓት መከበር ይኖርበታል፡፡
  • 3 የእስልምና እምነት ተከታይ ሴት ተማሪዎች ከዩኒፎርም ጋር የሚመሳሰል “ሂጃብ” ማድረግ ይችላሉ፤ ከሂጃብ በቀር ሙሉ ጥቁር ልብስ ሙሉ በሙሉ ፊትንም ጨምሮ የሚሸፍን ወይም “ኒቃብ” በትምህርት ተቋማት መልበስ አይፈቀድም፡፡
  • 4 የክርስትና እምነት ተከታይ መነኮሳት፤ መነኮሳያይት እና ካህናት እንዲሁም የእስልምና ተከታይ ሼኮች ብቻ በትምህርት ተቋማት ቆብ ሊያደርጉ ወይም ሻሽ ሊጠመጥሙ ይችላሉ፡፡
  • 5 በተራ ቁጥር 6.2፤ 6.3፤ 6.4 የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆነው፤ የትምህርት ተቋማት በሚያዘጋጁት ክብረ በዓል ወይም ተመሳሳይ ጉዳዮች ምክንያት በተቋሙ አስተዳደር ሃይማኖታዊ አለባበሶች ካልተፈቀዱ በስተቀር በማንኛውም መልኩ የማንኛውንም የሃይማኖት የአለባበስ ስርዓት በትምህርት ተቋማት መልበስ አይፈቀድም፡፡
  • 6 በተራ ቁጥር 6.2፤ 6.3፤ 6.4 የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆነው፤ በተለየ ሁኔታ የትምህርት ተቋሙ አስተዳደር (በሀዘን፣ በህመም ወዘተ) ከሚፈቅደው በስተቀር ተማሪዎች በመማሪያ ክፍል ውስጥ ነጠላ፣ ጋቢ ወዘተ… መልበስ ሻሽ መጠምጠምና ቆብ ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን ለማውጣት የስልጣኑን ምንጭ በጊዜው ፀንቶ የነበረውን የኢትዮዽያ ፌደራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ ቁ. 471/1998 እንደሆነ ይጠቅሳል፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 14 የትምህር ሚኒስቴር የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ተሰጥቶታል፡፡

  1. የትምህርት ስልጠና ስታንዳርድ ያወጣል፡፡ ሥራ ላይ መዋሉንም ያረጋግጣል፡፡
  2. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ፣

ሀ) አጠቃላይ የስርዓተ ትምህርት ማእቀፍ ያዘጋጃል፡፡

ለ) ለአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ መምህራን አነስተኛውን የትምህርት ብቃት መለኪያ ያወጣል፡፡

ሐ) በሙያና ቴክኒክ ዘርፍ የሙያ ስልጠና ደረጃና የብቃት ማረጋገጫ ደረጃ ያወጣል፡፡

መ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሊያሟሉ የሚገባቸውን አነስተኛውን ደረጃ ያወጣል፡፡

  1. የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ያቋቁማል፣ ያስፋፋል፤ ዕውቅና ይሰጣል፣ ጥራትና አግባብነት ያለው ትምህርት መስጠታቸውን ይቆጣጠራል፡፡
  2. ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተ አገራዊ የአህዝቦት (በእንግሊዝኛው ቅጂ ‘popularization’) ተግባሮችን ያከናውናል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት ስልጣንና ተግባራት መመሪያውን ለማውጣት ስልጣን እንደሚያጎናጽፉ ድምዳሜ ከመያዙ በፊት አንድ መሰረታዊ ነጥብ መነሳት ይኖርበታል፡፡ ይኸውም፤ ማንኛውም መ/ቤት ከተቋምነቱ ወይም ከአጠቃላይ ስልጣንና ተግባራቱ የመነጨ መመሪያ የመደንገግ ስልጣን (inherent rulemaking power) የለውም፡፡ እያንዳንዱ ተቋም የስልጣኑ ምንጭ የተወካዮች ም/ቤት ውክልና እንደሆነ መቼም መዘንጋት የለበትም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ሊጠቅስ የሚገባው ውክልና የሰጠውን የህግ ድንጋጌ ነበር፡፡ ስለሆነም ውክልና በሌለበት በትምህርት ተቋማት የአምልኮ ስርዓትን በሚመለከት መመሪያ መደንገግ ከስልጣን በላይ የሆነ ተግባር በመሆኑ መመሪያው የህጋዊነት መስፈርት አያሟላም፡፡

በተጨማሪም የአዋጅ ቁ. 471/1998 አንቀጽ 14 ድንጋጌ ይዘት የአምልኮ ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንዲወሰን አይፈቅድም፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መመሪያው በክልል መንግስታት ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ጭምር አካቷል፡፡ በመመሪያው የትርጓሜ ክፍል የትምህርት ተቋማት የተባሉት ከመዋዕለ ህጻናት እስከ ዩኒቨርስቲ ድረስ ያሉትን በሙሉ ያጠቃልላል፡፡ የሕዝብ ትምህርት ቤቶችን አመራርና አስተዳደር፣ የትምህርት አሰጣጥ፣ የመምህራን አቀጣጠርና አስተዳደር በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴር ስልጣን የትምህርት ቤቶችን አመራርና አስተዳደር ለማጠናከር በወጣ (ማሻሻያ) አዋጅ ቁ. 217/1992 አንቀጽ 1 ተሽሮ ለብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት እና የአዲስ አበባና ድሬዳዋ መስተዳድሮች ተላልፏል፡፡ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የአምልኮ ስርዓቱን በተመለከተ በህግ መወሰን/ያለመወሰን ስልጣኑም የእነዚህ አካላት ነው፡፡

 2. የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሠራተኞች አስተዳዳር

ፍትህ የማግኘት መብትን የሚደነግገው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀፅ 37/1/ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ለሌላ በህግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት መብት አለው፡፡

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሰራተኞች አስተዳደር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 155/2000 በልዩ ሁኔታ ሰራተኞችን ማሰናበትን በተመለከተ በአንቀጽ 37 እንደሚከተለው ደንግጓል፡፡

1) በዚህ ደንብ በሌላ ሁኔታ የተደነገገው ቢኖርም ዋና ዳይሬክተሩ በሙስና የተጠረጠረንና እምነት ያጣበትን ሰራተኛ መደበኛውን የዲስፕሊን አፈፃፀም ስርዓት ሳይከተል ከስራ ማሰናበት ይችላል

2) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ከስራ የተሰናበተ ሰራተኛ በየትኛውም የፍርድ አካል ውሳኔ ወደ ስራ መመለስ አይችልም

የህገ መንግስቱና የደንብ ቁ. 155/2000 ድንጋጌዎች በስም (አንቀጽ ቁጥር) ይመሳሰላሉ፡፡ በተግባር ግን ተጻራሪ ናቸው፡፡ የመጀመሪያው መብት ያናጽፋል፤ ሁለተኛው ይነፍጋል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ህገ መንግስቱን የማክበርና የማስከበር ግዴታ ከተጣለባቸው አካላት መካከል አንደኛው ነው፡፡ በዚህ ግዴታው የህግ አውጭነት ስልጣኑ ምንጭ የሆነው ህግ ያሰመረለትን ወሰን ሊያከብር ይገባል፡፡ ምክር ቤቱ ደንብ ቁ. 155/2000 ለማውጣት ህግ እንደፈቀደለት የሚጠቅሰው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ አዋጅ ቁ. 587/2000 አንቀጽ 19/1/ ለ ድንጋጌ ነው፡፡ ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

[የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን] ሠራተኞች አስተዳደር የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ ይመራል፡፡

በስልጣን ምንጭነት የተጠቀሰው ህግ ም/ቤቱ በሠራተኞች አስተዳደር በተመለከተ ደንብ እንዲያወጣ ይፈቅድለታል፡፡ ይሁን እንጂ ሠራተኞች በጥርጣሬ እንዲሰናበቱና በየትኛውም የፍርድ አካል መብቸውን እንዳይጠይቁ የሚከለክል ኢ-ህገ መንግስታዊ ደንብ እንዲያወጣ ስልጣን አልሰጠውም፡፡

 3. የህብረህዋሳት ልገሳና ንቅለ ተከላ

የመድሀኒት፣ የምግብና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ደንብ ቁ. 299/2006 አንቀጽ 58-62 ድንጋጌዎች ስለ ደምና ደም ተዋጾ እና የሰውነት አካል ክፍሎችና የህብረህዋሳት ልገሳና ንቅለ ተከላ (donation of blood and blood products and donation and transplantation of organs and tissues) የሚከናወንባቸውን ሁኔታዎች ይደነግጋሉ፡፡ ደንቡ የወጣው የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁ. 661/2002 አንቀጽ 55/1/ እና አሁን በአዋጅ ቁ. 916/2008[2] በተተካው አዋጅ ቁ. 691/2003[3] አንቀጽ 5 ለሚኒስትሮች ምክር ቤት በተሰጠ ስልጣን እንደሆነ በመግቢያው ላይ ተመልክቷል፡፡ አዋጅ ቁ. 661/2002 የአካላት ልገሳና ንቀለ ተከላ የሚመለከት ድንጋጌ አልያዘም፡፡ አንቀጽ 55/1/ ም/ቤቱ የሰጠው ስልጣን አዋጁን ለማስፈጸም የሚረዱ ደንቦች እንዲያወጣ ብቻ ነው፡፡ አዋጁ በዝምታ ያለፈውን ለዛውም ንቀለ ተከላን የሚያክል ትልቅ አገራዊ ጉዳይ በማስፈጸም ሰበብ በደንብ መወሰን የፓርላማን ቦታ መቀማት እንጂ በውክልና ህግ የማውጣት ተግባር (delegated legislation) አይደለም፡፡

እንደ ተጨማሪ የስልጣን ምንጭ የተጠቀሰው የአዋጅ ቁ. 691/2003 አንቀጽ 5 ትንሽ አግራሞት መፍጠሩ አይቀርም፡፡ ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 77 የተመለከተው ይሆናል፡፡

ህገ መንግስት ጠቅሶ ህግ ማውጣት የሚችለው የተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ነው፡፡ በአንቀጽ 77 ንዑስ አንቀጽ 13 እንደሰፈረው የሚኒስትሮች ም/ቤት የተወካዮች ም/ቤት በሚሰጠው ስልጣን መሰረት ደንብ የማውጣት ስልጣን አለው፡፡ ስልጣን በማስተላለፍ የሚፈጠረው የወካይ-ተወካይ ግኝኑነት ሚኒስትሮችን ከአስፈጻሚነት በተጨማሪ የህግ አውጭነት ሚና ያላብሳቸዋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ በውክልና የተላለፈ ስልጣን በሌለበት የሚወጣ ማንኛውም ደንብ የህጋዊነትና ህገ መንግስታዊነት ገደቦችን ይጥሳል፡፡

ከላይ በምሳሌነት የተጠቀሱት አስተዳደራዊ ድንጋጌዎች አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን የህጋዊነትና የህገ መንግስታዊነት ችግር ያንጸባርቃሉ፡፡ ውጤታማ የቁጥጥር ስልቶች ባልተረዘጉበት ሁኔታ በየጊዜው የሚወጡት መመሪያዎችና ደንቦች በስም ‘የበታች ህጎች’ በተግባር ግን ‘የበላይ ህጎች’ መሆናቸው አይቀርም፡፡

 4. የባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ አባልነት

በሰ/መ/ቁ. 44226 (አመልካች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ተጠሪዎች እነ ህብረት ኢንሹራንስ ኩባንያ /3 ሰዎች/ ታህሳስ 15 2003 .. ቅጽ 11) የአመልካች መመሪያ ከፊል ድንጋጌዎች ስልጣን የሰጠውን አዋጅ ስለሚቃረኑ ተፈጻሚነት እንዳይኖራቸው በተጠሪዎች ክስ ቀርቦ በፌደራል መጀመሪያ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች እንዲሻሩ ተወስኗል፡፡ ተቃውሞ የቀረበበት መመሪያ እ.ኤ.አ. 2006 ዓ.ም. የወጣው Directive No. SBB/39/2006 Licensing and Supervision of Banking Business፡ Amendment for New Bank Licensing and Approval of Directors and CEO ሲሆን የባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ አባል በተመሳሳይ ጊዜ በሌላ የገንዘብ ተቋም የቦርድ አባል ሆኖ እንዳያገለግል፣ 75 ፐርሰንት አባላት የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲኖራቸው እንዲሁም በድጋሚ መመረጥ እንዳይችሉ የተለያዩ ገደቦችን ይጥላል፡፡ ባንኩ መመሪያውን ያወጣው በጊዜው ጸንተው በነበሩት የገንዘብና ባንክ አዋጅ ቁ. 83/1986 አንቀጽ 41 እና የባንክ ስራ ፈቃድና ቁጥጥር አዋጅ ቁ. 84/1986 አንቀጽ 36 እንደሆነ በመመሪያ መግቢያ ላይ ተገልጿል፡፡

ጉዳዩ በሰበር ሲታይ ባንኩ መመሪያውን ለማውጣት ስልጣን እንዳለው በተደረሰበት ድምዳሜ መሰረት የስር ፍ/ቤቶች ውሳኔዎች ተሽረዋል፡፡ ሆኖም ለስልጣኑ ምንጭ ችሎቱ የጠቀሳቸው ድንጋጌዎች ባንኩ ራሱ በመመሪያው ላይ ካሰፈራቸው ይለያሉ፡፡ ችሎቱ ለህግ ትርጉሙ ድጋፍ ያደረገው የባንኩን የመቆጣጠር ስልጣን እና በሁለቱም አዋጆች በጥቅል የተነገው ባንኩ አዋጆቹን ለማስፈጸም የተሰጠው መመሪያ የማውጣት ስልጣን ነው፡፡

የማስፈጸም ዓለማ ያለው መመሪያ በሚያስፈጽመው አዋጅ ላይ ከተደነገጉ ጉዳዮች በላይ አልፎ ሊሄድ አይችልም፡፡ የመቆጣጠር ስልጣን እንዲሁ በህጉ ከተዘረጋው የቁጥጥር ማዕቀፍ ሊያፈነግጥ አይገባም፡፡ የመቆጣጠርና የማስፈጸም ስልጣን ብቻውን መመሪያውን ህጋዊ የሚያደርገው ከሆነ በባንኩ መመሪያ የማውጣት ስልጣን ላይ ምንም ዓይነት ገደብ ማስቀመጥ አይታሰብም፡፡ በዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ላይ የሚደረጉ ገደቦችን በመመሪያ ለመወሰን መጀመሪያ ዋናው ህግ መሰረታዊ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ሊደነግግ ይገባል፡፡ የሰበር ችሎት ያንጸባረቀው አቋም ማናቸውንም የባንኩን መመሪያዎች ህጋዊነት ያለጥያቄ አስቀድሞ የማጽደቅ ያክል ነው፡፡

[1] በትምህርት ተቋማት የአምልኮ ስርዓትን በሚመለከት የወጣ መመሪያ፡ የትምህርት ሚኒስቴር ህዳር 2000 ዓ.ም.

[2] የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ስራ አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር መወሰኛ አዋጅ ቁ. 916/2008

[3] የኢትዮዽያ ፌደራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ ቁ. 691/2003


Filed under: Articles, Constitution and Human rights, Constitutional law, Directives, Education law, National Bank of Ethiopia

ይርጋ፡ ማንሳት መተው መቋረጥ እና መነሻ ጊዜ

$
0
0

ይርጋ

በህግ ተለይቶ ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ በኋላ በአንድ ጉዳይ ክስ ለማቅረብ የሚከለከልበት የህግ ፅንሰ-ሃሳብ

ይርጋ አንድ ሰው በጉዳዩ ላይ መብት ያለው ቢሆንም እንኳን ይህንን መብቱን ለመጠየቅ የማይችልበትን ገደብ የሚመለከት ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 44800 ቅጽ 10[1]

የይርጋ ህግ መሰረታዊ አላማ ተገቢውን ጥረት የሚያደርጉ ገንዘብ ጠያቂዎችን ወይም መብት አስከባሪዎችን መቅጣት ሳይሆን መብታቸውን በተገቢው ጊዜ ለመጠየቅ ጥረት የማያደርጉትን ሰዎች መቅጣት መሆኑ ይታመናል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 98358 ቅጽ 17[2]

የይርጋ መቃወሚያ ማንሳት

ክሱ በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን በመግለጽ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ /በተከሳሽ/ ማቅረብ

የይርጋ ደንብ ተፈጻሚ የሚሆነው ክስ ከቀረበ በኋላ ተከሳሹ የይርጋ መቃወሚያ አንስቶ የተከራከረ ከሆነ ነው፡፡ ከሳሽ ክስ የማቅረብ መብቱ በይርጋ ቀሪ ከሆነ በኋላ ክስ አቅርቦ ተከሳሽ ክሱ በይርጋ ቀሪ መሆኑን በመግለጽ ካልተቃወመ ክሱ ተቀባይነት አግኝቶ መታየት ይቀጥላል፡፡ የጊዜ ገደቡ በማለፉ ብቻ ፍ/ቤት ይርጋውን በራሱ አነሳሽነት አንስቶ ክሱን ውድቅ ሊያደርግ አይችልም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 44800 ቅጽ 10[3]

በመርህ ደረጃ የይርጋ ጥያቄ በተከራካሪዎች ካልተነሳ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያነሳው አይችልም፡፡ የይርጋን ጉዳይ የማንሳት ወይም ያለማንሳት ኃላፊነት ሙሉ በሙሉ የተከሳሽ ወገን ነው፡፡ ይህ አጠቃላይ መሰረተ ሀሳብ ግን ባልተነጣጠለ ኃላፊነት በተከሰሱ ተከሳሾች ላይ ተፈጻሚነት የለውም፡፡ በዚህን ጊዜ በአንደኛው ተከሳሽ የሚነሳ የይርጋ መቃወሚያ ክሱን በይርጋ ቀሪ የሚያደርገው ቢሆን መቃወሚያው በሁሉም ተከሳሾች እንደተነሳ ተቆጥሮ ክሱ ውድቅ መደረግ ይኖርበታል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 19081 ቅጽ 4፣[4] ፍ/ህ/ቁ. 1677፣ 1901

ተከራካሪዎች የይርጋ ጥያቄ እስካቀረቡ ድረስ ጥያቄውን በትክክለኛው አንቀጽ መሰረት እንዲመራ ማድረጉ የፍርድ ቤት ሃላፊነት ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 17937 ቅጽ 4፣[5] ፍ/ህ/ቁ. 1000፣ 1677፣ 1845

የይርጋ ደንብ አንድ ክስ በፍርድ ቤት ቀርቦ በስረነገር እንዳይታይ የሚከለክል ሲሆን የሕሊና ግምት (በ2024 የሰፈረው የመክፈል ግምትን ጨምሮ) በሌላ በኩል የማስረዳት ሸክምን ከአንድ ወገን ወደ ሌላው የማስተላለፍ ውጤት ብቻ ያለው በመሆኑ ከሣሽ ያቀረበውን ክስ ይዘት መርምሮ ውሣኔ መስጠትን የሚከለክል አይደለም፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ ውስጥ የሰፈረውን ይርጋ ተከሣሹ ወገን ካላነሳው ፍርድ ቤቱ በራሱ ሊያነሳ እንደማይችል በፍትሐብሔር ሕግ ቁ.1856 የተጠቀሰ ቢሆንም ይህ ድንጋጌ ተፈጻሚነት የሚኖረው ለይርጋ ድንጋጌዎች እንጂ በሕግ ግምት የማስረዳት ሸክም ከአንድ ተሟጋች ወደ ሌላው በሚዘዋወርባቸው ሁኔታዎች አይደለም፡፡

በመሆኑም ይርጋን (Period of limitation) ከሕግ ግምት (Presumptions) ጋር በማመሳሰል ለይርጋ ተፈፃሚ የሚሆነው ሕግ ለህግ ግምትም ተፈፃሚ መሆን ይገባዋል በማለት የሚቀርብ ክርክር የህጉን መንፈስ፣ ዓላማና ግልጽ ይዘት ያልተከተለ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 17068 ቅጽ 1[6]

ይርጋ መተው

አንድ ሰው የይርጋ ጊዜውን ትቶታል የሚባለው ለዕዳው ምንጭ የሆነውን ግዴታ በማመን አዲስ መተማመኛ ሰነድ የሰጠ እንደሆነ ነው፡፡ ይርጋን መተው ውጤቱ ይርጋን የሚያቋርጥ ሳይሆን አዲስ የይርጋ ጊዜ መቆጠር እንዲጀምር ያደርጋል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 90361 ቅጽ 6[7]

ይርጋ መቋረጥ

በፍ/ብ/ሕ/ቁ/1852 ድንጋጌ መሠረት ይርጋ በተቋረጠ ጊዜ ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ እንደገና አዲስ የይርጋ ዘመን መቁጠር እንደሚጀምር በዚሁ ድንጋጌ በንዑስ ቁጥር /1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የሚቻለው ይርጋው በተቋረጠ ጊዜ ቀድሞ የነበረው የይርጋ ጊዜ እንደ አዲስ መቁጠር የሚጀምር መሆኑን ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 31185 ቅጽ 6[8]

በሕግ ተለይቶ የተወሰነ የይርጋ ጊዜ የመቋረጥ እና ያለመቋረጥ ጉዳይ አከራካሪ ነጥብ ሆኖ ሊነሳ የሚችለው የይርጋውን መቆጠር ያቋርጠዋል የተባለው ምክንያት የተከሰተው የይርጋው ጊዜ ከመሙላቱ በፊት በሆነ ጊዜ እንጂ የይርጋው ጊዜ የሞላ ወይም ያለፈ በሆነ ጊዜ ጭምር አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 90361 ቅጽ 6[9]

ክስ የማቅረብ ውጤት

ስልጣን ለሌለው የዳኝነት አካል ክስ ማቅረብ ይርጋን ያቋርጣል፡፡

(በመዝገብ ቁጥር 16648 ስለ ይርጋ ጊዜ አቆጣጠርና ስለ ይርጋ መቋረጥ የተሰጠው የሕግ ትርጉም ተለውጧል፡፡)

ሰ/መ/ቁ. 36730 ቅጽ 9[10]

ክስ የማቅረብ ውጤት /ሽያጭ ውል/

ይርጋ ከሚቋረጥባቸው ምክንያቶች አንደኛው ባለገንዘቡ መብቱ እንዲታወቅለት በፍ/ቤት ክስ አቅርቦ ለባለእዳው አስታውቆ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 43992 ቅጽ 10፣[11] ፍ/ህ/ቁ. 1851(ለ)

ክሱ የቀረበው መብቱን በሚጠይቀው ባለገንዘብ ባይሆንም ባለዕዳው በባለገንዘቡ ላይ ያቀረበው ክስ በይዘቱ የይርጋ መቃወሚያ ከተነሳበት ክስ ጋር ተያያዥነት ካለው ይርጋውን ያቋርጠዋል፡፡

የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢ ንብረቱን ለመረከብ (የሽያጭ ውሉ እንዲፈጸምለት) ያቀረበው ክስ ከሽያጭ ውሉ ቀን ጀምሮ ሲቆጠር በይርጋ የሚቋረጥ ቢሆንም ሻጭ ቀደም ብሎ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስለት ክስ ካቀረበ በገዢው ላይ ተፈጻሚ የሚሆነውን የይርጋ ጊዜ ያቋርጠዋል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 43636 ቅጽ 10[12]

በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1776 እና በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 ድንጋጌዎች መሠረት የቤት ሽያጭ ውል ይፈጸምልኝ ክስ ሲቀርብ በሕግ የተደነገገው የይርጋ ሕግ የጊዜ ገደብ አልፏል ወይስ አላለፈም? የሚለውን ነጥብ ለመወሰን በመጀመሪያ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ እንደዚሁም ድንጋጌው ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2875 መሠረታዊ መርህና ስለ ሽያጭ እና ጠቅላላ ውል ከተደነገጉ ድንጋጌዎች ጋር ሊኖረው የሚገባውን ተፈፃሚነት መመርመር ያስፈልጋል፡፡

  1. የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2893 ንዑስ አንቀጽ 3 “ስለሆነም ሻጭ ውሉን እንደውሉ ቃል ለመፈፀም መዘግየቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ውሉ እንዲፈፀምለት ካልጠየቀ በቀር ገዢው ውሉ በግዴታ እንዲፈፀም የማድረግ መብቱን ያጣል” በማለት ይደነግጋል፡፡ እዚህ ላይ በአማርኛው “መዘግየቱን ከተረዳበት” በሚለውና በእንግሊዘኛው “ascertained” በሚለው ቃል መካከል ልዩነት ያለመሆኑን ለመገንዘብ እንችላለን፡፡ የድንጋጌው መንፈስ ገዥ በአንድ ዓመት ውስጥ ውሉ እንዲፈፀምለት ለፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ያለበት ሻጭ በሽያጭ ውሉ መሠረት ለመፈፀም ፈቃደኛ አለመሆኑን ካረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ እንደሆነ የእንግሊዘኛውን የቃል አጠቃቀም በማየት ለመረዳት ይቻላል፡፡

እዚህ ላይ የሚነሣው ጥያቄ ሻጭ በሽያጭ ውሉ መሠረት ለመፈፀም እንደማይፈልግ ገዥ ያረጋገጠ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ ያለበት ማን ነው? የሚለው ነው፡፡ ለዚህ መሠረታዊ ነጥብ እልባት ለመስጠት ስለውል እና ተዋዋይ ወገኖች በፍትሐብሔር ሕጉ የተቀመጠ የሕግ ግምቶችን ማየት አስፈላጊ ነው፡፡

  1. በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ውሎች ባቋቋሟቸው ሰዎች ላይ ሕግ ናቸው በማለት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1731ንዑስ አንቀጽ 1 የደነገገ ሲሆን ውሎች በተዋዋይ ወገኖች መካከል ሊኖር የሚገባውን የቅንነት የመተማመን ግንኙነት መሠረት በማድረግ በቅን ልቦና ሊተረጎሙ እንደሚገባ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1732 ይደነግጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ስናየው ተዋዋይ ወገኖች በተዋዋሉት የውል ቃል መሠት ውሉን የመፈፀም ፍላጎትና ቅን ልቦና ያላቸው መሆኑ የውል ሕግ ግምት የሚወስድበት ጉዳይ በመሆኑ ገዥ ሻጭ በሽያጭ ውሉ በገባው የውል ቃል መሠረት እንደሚፈጽም የተለያዩ የተስፋ ቃሎችን ሲሰጠው የቆየ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ የለበትም፡፡

በተቃራኒው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ድንጋጌን ጠቅሶ የሚከራከር ሻጭ ከገዥ ጋር ባደረገው የቤት ሽያጭ ውል መሠረት ለመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን ገዥ በማያሻማ ሁኔታ እንዲያውቅ እና እንዲረዳው ያደረገ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለበት፡፡ ሻጭ በውሉ መሠረት ለመፈፀም እንደማይፈልግ በእርግጠኝነት ገዥ እንዲያውቅ ካደረገው ከአንድ ዓመት በኋላ የሽያጭ ውሉ በፍርድ ኃይል እንዲፈፀምለት የጠየቀ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለበት፡፡ ስለሆነም የማይንቀሣቀስ ንብረት የሸጠ ሰው ሻጭ በሽያጭ ውሉ መሠረት የቤቱን ይዞታና የባለቤትነት ሰነዶች ለገዥ ያላስረከበ ከሆነ ውሉን ለመፈፀም ፈቃደኛ አለመሆኑንና በጽሑፍና በማያሻማ ሁኔታ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1789 ንዑስ አንቀጽ 3 በሚደነግገው አይነት ለገዠ ካሣወቀው ከአንድ ዓመት በኋላ የውል ይፈፀምልኝ ክስ ያቀረበ መሆኑን ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡

ሻጭ በውሉ መሠረት የቤቱን ይዞታና የባለቤትነት ሰነዶች ለገዥ አስተላልፎ ከሆነ ገዥ ሻጭ በውሉ መሠረት ይፈጽማል የሚለውን ዕምነት የሚያጠናክርና ውሉም በከፊል መፈፀም መጀመሩን የሚያሣይ መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2875 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2274 ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡ ሰለሆነም ሻጭ የቤቱን ባለሀብትነት ለገዥ ለማስተላለፍ እንደማይፈልግና የቤቱን ይዞታ ሻጭ በመልቀቅ እንዲያስረክበው የከፈለውንም ገንዘብ ገዥ እንዲወስድ በማያሻማ ሁኔታ የፍትብሔር ሕግ ቁጥር 1789 ንዑስ አንቀጽ 3 በሚደነግገው አይነት ለገዥ ያሣወቀ መሆኑን ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡

ሻጭ የቤቱን ሰነዶች ለገዥ አስተላልፎ የቤቱን ይዞታ ይዞ በሚገኝበት ጊዜ የቤቱን ሰነዶች ሻጭ እንዲመልስለት የከፈለውን ገንዘብ እንዲወስድ በማያሻማ ሁኔታና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1789 ንዑስ አንቀጽ 3 በሚደነግገው አይነት ለገዥ ያሣወቀ መሆኑን ማስረዳት የሚጠበቅበት ሲሆን ከላይ ከተጠቀሱት ሁኔታዎች በአማራጭ ሻጭ ውሉ እንዲፈርስለት ወይም እንዲሰርዝለት በፍርድ ቤት ክስ አቅርቦ በውሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን ገዥ እንዲረዳው ከተደረገ ከአንድ ዓመት በኋላ የውል ይፈፀምልኝ ክስ ገዥ ያቀረበ መሆኑን ወይም በሕግ እውቅና ላለው የሽምግልና ተቋም ሻጭና ገዥ በነበራቸው ድርድር ሻጭ ውሉን ለመፈፀም እንደማይፈልግ ገዢ  እንዲረዳው ከተደረገ ከአንድ ዓመት በኋላ ክሱን ያቀረበው መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለበት፡፡ በአጠቃላይ ሻጭ በገባው የሽያጭ ውል ቃል መሠረት ለመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ለገዥ ካሣወቀውና ገዥም ይህንኑ ከተረዳና ካረጋገጠ ከአንድ ዓመት በኋላ የውል ይፈፀምልኝ ክስ ገዥ ያቀረበ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለበት፡፡

ሻጭ በውሉ መሠረት ለመፈፀም የማይፈልግ መሆኑን ገዥ ያረጋገጠ መሆኑን ገዥ ውሉ እንዲፈፀምለት ማስጠንቀቂያ መስጠቱንና ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ሻጭ በውሉ መሠረት አለመፈፀሙን በማየት ብቻ ለማረጋገጥ አይችልም፡፡ ሻጭ ገዥ ማስጠንቀቂያ ከሰጠው በኋላም ቢሆን የተለያዩ ችግሮችን እያነሣ በመካከላቸው ያለውን የመተማመንና የቅን ልቦና ግንኙነት ተጠቅሞ ከአንድ ዓመት በላይ ውሉን ሣይፈፅም የሚቆይበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡

ስለዚህ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ይርጋ ተፈፃሚነት የሚኖረው ገዥ ለሻጭ ማስጠንቀቂያ የሰጠበትን ቀን መነሻ በማድረግና ጊዜውን በማስላት ሣይሆን ሻጭ በውሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ገዥ እንዲያውቀው ያደረገበትን ቀን መነሻ በማድረግ መሆን ይገባዋል፡፡

  1. በሁለተኛ ደረጃ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚነት የሚኖረው በሻጭና በገዥ መካከል የተደረገው ውል የማይፈፀምበት የመጨረሻ ቀን በጥብቅ የተወሰነ ከሆነ በውሉ የተወሰነ የጊዜ ገደብ ካለፈ ከአንድ ዓመት በኋላ ገዥ የውል ይፈፀምልኝ ክስ ማቅረቡን በማስረዳት እንደሆነ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2875 መሠረታዊ መርህና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 ድንጋጌዎች ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2331ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 ድንጋጌዎች ጋር አጣምሮ በማየት ለመረዳት ይቻላል፡፡
  2. በሶስተኛ ደረጃ የሚነሣው ጥያቄ በዚህ ጉዳይ ተጠቃሽና ተፈፃሚ መሆን ያለበት የይርጋ ሕግ ድንጋጌ የትኛው ነው? የሚለው ነው፡፡ ሻጭ በውሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን ለገዥ በማያሻማ ሁኔታ ያሣወቀ መሆኑን ባላስረዳበት ሁኔታ ወይም የሽያጭ ውሉ የሚፈፀምበትን ጥብቅ የጊዜ ገደብ ባልተገለፀበት ሁኔታ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 የተደነገገው የአንድ ዓመት የይርጋ የጊዜ ገደብ ተፈፃሚነት የለውም፡፡ በልዩ የሕግ ድንጋጌ የተቀመጠዉ የይርጋ ጊዜ ገደብ ተፈፃሚነት በማይኖረው ጊዜ ወይም በልዩ ሁኔታ የተደነገገ የይርጋ የጊዜ ገደብ ከሌለ ውል ይፈፀምልኝ በሚል መነሻ የሚቀርቡ ክርክሮች ላይ ተፈፃሚት ያለው የይርጋ ሕግ ድንጋጌ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1845እንደሆነ ይህንን ድንጋጌ ይዘት በመመርመር ለመረዳት ይቻላል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 38935 ቅጽ 8[13]

ሻጭ የውል ይፍረስልኝ ክስ ለፍርድ ቤት ማቅረቡ ውሉን ለመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን ለገዢ በማያሻማ መንገድ ከማሣወቅ ያለፈ ምክንያትና ውጤት ያለው ተግባር ነው፡፡ ሻጭ ውሉ እንዲፈርስ ሲጠይቅ ውሉ ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለማቋቋም የማያስችሉ ጉድለቶች ያሉበት በሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች እንደ ሕግ ሆኖ ሊገዙበት የማይገባ መሆኑን የሚያሣዩ የውሉን ሕልውና ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባና የውል ሕጋዊነት በፍርድ ቤት ተመርምሮ ፈራሽ እንዲባል ወይም እንዲሠረዝ የሚቀርብ ነው፡፡ የውሉ ሕጋዊነትና ሕልውና ጥያቄ ተነስቶበት በፍርድ ቤት በሚመረመርበት ጊዜ ሂደት ገዢ ውሉ ሕጋዊ መሆኑን ከማሣየትና ከማስረዳት አልፎ ውሉ በግዳጅ እንዲፈጽምለት የመጠየቅ ግዴታ አይኖርበትም፡፡

ከዚህ አንፃር ውሉ በፍርድ ቤት ፈራሽ እንዲሆን ወይም እንዲሰረዝለት በውሉ የሚገደድበት ሁኔታ ይቋረጣል፡፡ በሌላ በኩል በክርክሩ ከተረታ ገዢ ሕጋዊ ተፈፃሚነትና አስገዳጅነት ባለው ውሉ ንብረቱን የገዛ መሆኑ ከሻጭ ጋር ባደረገው የውል ሰነድ ብቻ ሣይሆን በፍርድ ቤት ውሣኔ የተረጋገጠለት የፍርድ ባለመብት ይሆናል፡፡ ስለሆነም ገዢ ፍርድ ቤቱ ሕጋዊነቱንና አስገዳጅነቱን መርምሮ በፍርድ ያረጋገጠውን ውል እንዲፈጽምለት ሻጭን የመጠየቅ መብቱ በፍርድ ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 384/ሀ/ በተደነገገው አስር ዓመት ጊዜ ውስጥ እንጂ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀጽ 3 በተደነገገው የአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ የሚገደብ አይደለም፡፡ ስለዚህ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2892 ንዑስ አንቀስ 3 የተቀመጠው የጊዜ ገደብ በዚህ ጉዳይ አግባብነት የለውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 39725 ቅጽ 8[14]

ይርጋ መነሻ ጊዜ(የ—)

ይርጋ መቆጠር የሚጀምርበት ጊዜ

የይርጋ ቀን መቆጠር የሚጀምረው ግዴታውን ለመጠየቅ ተገቢ ከሆነው ወይም ውሉ የሚሰጠው መብት ከተሰራበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡

የሥራ ውል የተቋረጠበትና የስንብት ደብዳቤ የተሰጠበት ቀን ከተለያየ ይርጋ መቆጠር የሚጀምረው ደብዳቤው ለሠራተኛው ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 94931 ቅጽ 16፣[15] ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1846

በፍትሐ ብሔር ስነ-ስርዓት ህጉ የሚገኙት የጊዜ ገደቦች አቆጣጠር የሚመራው በፍትሐ ብሔር ህግ ባሉት የጊዜ አቆጣጠር ደንቦች ነው፡፡

ጉዳዩ በሌለበት ታይቶ ውሳኔ የተሰጠበት ወገን ውሳኔው እንዲነሳለት በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 78/1/ መሰረት በአንድ ወር ውስጥ የሚያቀርበው ጥያቄ የአንድ ወር ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ውሳኔ መሰጠቱን ከተረዳበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ቀን ለይርጋው ጊዜ መቆጠር መነሻ አይሆንም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 76601 ቅጽ 13፣[16] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 78/1/

በወራሾች መካከል ውርስ እንዲጣራ አቤቱታ መቅረብ ያለበት በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሲሆን ይህም ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው አንደኛው ወራሽ የውርሱን ንብረት በእጁ ካደረገበት እንጂ ስመ ሀብቱን በስሙ ካዞረበት ጊዜ ጀምሮ አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 52407 ቅጽ 11፣[17] ፍ/ህ/ቁ. 1000/1/

ከውርስ ሃብት ጋር በተያያዘ ወራሽ የሆነና አካለ መጠን ያልደረሰ ሰው ላይ የይርጋ ጊዜ ሊቆጠር የሚገባው አካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ አንስቶ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 57114 ቅጽ 11[18]

ይዞታን አስመልክቶ ከሚነሳ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ ጋር በተያያዘ ተፈፃሚ የሚሆነው የይርጋ ጊዜ መቆጠር ያለበት አቤቱታ አቅራቢው የይዞታ መብቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ከሚመለከተው አካል ካገኘበት ቀን ጀምሮ እንጂ አቤቱታ የቀረበበት ድርጊት መፈፀም ከጀመረበት ዕለት አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 60392 ቅጽ 11፣[19] ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1140፣ 1149፣ 1146/1/፣ 1144/2/

[1] አመልካች አቶ አብደራዛቅ ሀሚድ እና ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 05 ቀን 2002 ዓ.ም.

[2] አመልካች አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ እና ተጠሪ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ጥር 05 ቀን 2007 ዓ.ም.

[3] አመልካች አቶ አብደራዛቅ ሐሚድ እና ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 05 ቀን 2002 ዓ.ም.

[4] አመልካች አሊ ቃሌብ አህመድ እና ተጠሪ እነ አቶ ሚሊዮን ተፈራ /3 ሰዎች/ መጋቢት 18 ቀን 1999 ዓ.ም.

[5] አመልካች ወ/ሮ ድንቄ ተድላ እና ተጠሪ እነ አቶ አባተ ጫኔ መጋቢት 20 ቀን 1999 ዓ.ም.

[6] አመልካች የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና መልስ ሰጪ ሚ/ር ቢሮኒ አቲክፖ ሐምሌ 19 ቀን 1997 ዓ.ም.

[7] አመልካች የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እና ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግንቦት 12 ቀን 2000 ዓ.ም.

[8] አመልካች የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እና ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግንቦት 12 ቀን 2000 ዓ.ም.

[9] አመልካቾች እነ ወ/ሮ አለዊያ ዑመር /7 ሰዎች/ እና ተጠሪ አቶ ሐሺም ሁሴን የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም.

[10] አመልካች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይሌ ኮርፕሬሽን እና ተጠሪ አቶ አማረ ገላው ሀምሌ 30 ቀን 2002 ዓ.ም.

[11] አመልካች እነ አቶ ይሌማ አንበሴ /4 ሰዎች/ እና ተጠሪ እነ ወ/ሮ እመቤት መንገሻ /5 ሰዎች/ መጋቢት 6 ቀን 2002 ዓ.ም.

[12] አመልካች ወ/ሮ አሌማዝ ተሰማ እና ተጠሪ እነ አቶ በየነ ወ/ሚካኤሌ/2 ሰዎች/ መጋቢት 22 ቀን 2002 ዓ.ም.

[13] አመልካች እነ አቶ ወልደፃድቅ ብርሃኑ /2 ሰዎች/ እና ተጠሪ አቶ ስንታየሁ አያሌው መጋቢት 3 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም.

[14] አመልካቾች እነ ወ/ሮ ዓለምሸት ካሣሁን /3 ሰዎች/ እና ተጠሪ አቶ ሽመልስ እንዳለ ሐምሌ 23 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም.

[15] አመልካች ወ/ሮ ጥሩወርቅ መንግስቴ ተጠሪ የተገጣጣሚ ህንፃ አካላት ማምረቻ ድርጅት የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም.

[16] አመልካች አቶ ሽመልሽ አማረ እና ተጠሪ አቶ አማረ መኮነን ሰኔ 18 ቀን 2004 ዓ.ም.

[17] አመልካቾች እነ ወ/ሮ ውልታ ደስታ ወ/ማሪያም /2 ሰዎች/ እና ተጠሪ ወ/ሮ እቴቴ ደስታ ኅዳር 27 ቀን 2003 ዓ.ም.

[18] አመልካች ወ/ሮ ሃና ፀጋዬ እና ተጠሪ ወ/ት ጣዕሙ ደስታ ግንቦት 3 ቀን 2003 ዓ.ም.

[19] አመልካች አቶ ጌትነት የኔው እና ተጠሪ አቶ ኢዩብ ቢንያም ወ/ቢኒያም ታህሣሥ 26 ቀን 2003 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

‘እንዳልተሰጠ የሚቆጠር ውሳኔ’ ምን ዓይነት ነው?

$
0
0

በህግ አግባብ የተቋቋመ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ውሳኔ ከሰጠ በኋላ ለአፈጻጸም ሲቀርብ ውሳኔው እንዳልተሰጠ ተቆጥሮ አፈጻጸሙን በያዘው ፍርድ ቤት ዋጋ የሚያጣበት የህግ መሰረት አለ? ከሰበር ችሎት ውሳኔዎች ለመረዳት እንደሚቻለው አንድ ውሳኔ በሶስት መንገዶት እንዳልተሰጠ ሊቆጠር ይችላል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ የስረ ነገር የዳኝነት ስልጣን አለመኖር ነው፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱ በአንድ መዝገብ ላይ ይህን አቋም ቢያራምድም በሌሎች ሁለት መዝገቦች ላይ ግን ራሱን በመቃረን የስረ ነገር የዳኝነት ስልጣን የፍርድ ቤትን ውሳኔ እንዳልተሰጠ እንደማያስቆጥረው የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ሌሎቹ ሁለት መንገዶችና የችሎቱ ተቃርኖ የታየባቸው መዝገቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡

  1. የሥረ ነገር የዳኝነት ስልጣን በሌለው ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ

አንድ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ከማየቱ በፊት የስረ ነገር የዳኝነት ስልጣን ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ያለበት ሲሆን የስረ ነገር የዳኝነት ስልጣን በተከራካሪ ወገኖች ባይነሳም በማናቸውም የክርክር ደረጃ ፍርድ ቤቱ በራሱ ሊያነሳው የሚገባው ጉዳይ መሆኑ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 9 እና 231/1/ ሰ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዲይ ነው፡፡ የሥረ ነገር የዳኝነት ስልጣን በሌለው ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ ደግሞ በመርህ ደረጃ እንዳልተሰጠ የሚቆጠር ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 64703 ቅጽ 12፣[1] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 9፣ 231/1/ ሰ

  1. ችሎት ለማስቻል በህጉ የተቀመጠው የዳኞች ቁጥር ባልተሟላበት ሁኔታ የሚሰጥ ውሳኔ

ጉዳዮች በሥነ ሥርዓት ሕጉ መሠረት የሚመሩበት አይነተኛ አላማ ክርክሮችን ፍትሃዊ በሆነ እና ሥርዓት ባለው መንገድ በመምራት በአጭር ጊዜ እና በአነስተኛ ወጭ እንዲቋጩ ማድረግ ስለመሆኑ ይታመናል፡፡ ይህንኑ የሥነ ሥርዓት ሕጉን አላማ ለማሳካት ደግሞ በሕጉ የተመለከቱትን የስነ ሥርዓት ድንጋጌዎችን እንደየአግባብነታቸው መከተልን የግድ ይላል፡፡ በስነ ሥርዓት ሕጉ የተመለከቱት ድንጋጌዎችን እንደየአግባብነታቸው ያለመከተል በተከራካሪ ወገኖች መሰረታዊ መብት ላይ አሉታዊ ውጤት ማስከተሉ አይቀሬ ነው፡፡ ስለሆነም በስነ ስርዓት ሕጉ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ተፈፃሚነት ሊኖራቸው የሚገባው ለጉዳዩ አግባብነት ሲኖራቸው እንጂ በዘፈቀደ ሊሆን አይገባም፡፡

ድንጋጌዎቹ አግባብነት ያላቸው ስለመሆኑ ከመለየቱ በተጨማሪ በጉዳዩ ላይ ተገቢነት አለው የሚለውን ትዕዛዝ ወይም ውሣኔ የሚሰጠው ችሎትም በሕጉ አግባብ የተመለከተው የዳኞች ቁጥር የተሟላ ሊሆን ይገባል፡፡ በሕጉ አግባብ ሊሟላ የሚገባው የዳኞች ቁጥር ሳይሟላ የሚሰጠው ትእዛዝ ወይም ውሣኔ እንደተሰጠ የማይቆጠርና ሕጋዊ ውጤት ሊኖረው የሚገባ አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ 73696 ቅጽ 13[2]

  1. በሞተ ሰው ውክልና ክርክር ተደርጎ የተሰጠ ውሳኔ

በሞተ ሰው ስም ቀደም ብሎ የተሰጠን ውክልና በመያዝ የሚቀርብ ክስ፣ የሚደረግ ክርክር እና የሚሰጥ ውሣኔ ህጋዊ ዕውቅናና ውጤት ሊሰጠው የማይገባው ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 95587 ቅጽ 17፣[3] ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 57፣ ፍ/ህ/ቁ. 2232/1/

ከሰ/መ/ቁ. 64703 ጋር ተቃርኖ

አንድ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሣኔ በሕግ ከተሰጠው የስረ ነገር የዳኝነት ስልጣን ውጭ የሆነ ጉዳይ በማየት የሰጠው ቢሆንም፣ ይህ ውሣኔ በይግባኝ ታይቶ እንዲታረም ካልተደረገ በስተቀር በፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 212 በጉዳዩ ላይ አስገዳጅነት ያለውና የመጨረሻ ውሣኔ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 85718 ቅጽ 15[4]

በሕግ አግባብ በፍ/ቤት የተሰጠን ውሣኔ የሞራልን ወይም የሕሊናን አስተሳሰብ መሠረት በማድረግ ዋጋ አልባ ሆኖ እንዲቀር ማድረግ በየትኛውም መለኪያ ተቀባይነት የሚኖረው አይደለም፡፡

ሰበር መ/ቁ. 38041 ቅጽ 8[5]

[1] አመልካች ሻምበል ለታይ ገ/መስቀል እና ተጠሪ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 1 አስተዳደር ጽ/ቤት ሐምሌ 29 ቀን 2003 ዓ.ም.

[2] አመልካች ወ/ሪት ሃና አበባው እና ተጠሪ አቶ አብዱ ይመር /በሌለበት/ ሚያዝያ 9 ቀን 2004 ዓ.ም.

[3] አመልካች ወ/ሮ ሐዋ በከር እና ተጠሪ እነ አቶ ቶፊቅ መሀመድ 2 ሰዎች ጥቅምት 28 ቀን 2007 ዓ.ም.

[4] አመልካች አቶ ቴዎድሮስ አማረ እና ተጠሪ አቶ አዲሱ ፍሰሃ ሰኔ 03 ቀን 2005 ዓ.ም.

[5] አመልካች ታደሰ ገ/መስቀል ተጠሪዎች እነ ሙሉጌታ ዘካርያስ /7 ሰዎች/ መጋቢት 22 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment

ተከሳሽን የሚጠቅም ቅጣት- የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም

$
0
0

በወንጀል የተከሰሰ ሰው አዲስ የወንጀል ህግ ከመውጣቱ በፊት በተፈፀመ ወንጀል ከተፈረደበት እና ሆኖም ግን ወንጀሉ በተፈፀመበት ጊዜ ስራ ላይ ከነበረው ወንጀል ህግ ይልቅ አዲሱ ህግ ለተከሳሹ ቅጣትን የሚያቀልለትና ተከሳሹን የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ ይሄው በአዲሱ ህግ ላይ ያለው ቅጣት የሚፈጸምበት ስለመሆኑ ከወንጀል ህጉ ቁ. 6 ድንጋጌ ይዘት የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 95438 ቅጽ 6፣[1] ወ/ህ/ቁ. 6

የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ተፈጻሚነት

በአንድ ወንጀል ተመሳሳይ የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ ከተላለፈባቸው ተከሳሾች መካከል አንደኛው ባቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻነት ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው ፍርድ ከተሰጠ ፍርዱ የሰበር አቤቱታ ላልጠየቁት ሆነ ጠይቀው አቤቱታቸው በአጣሪ ችሎት አያስቀርብም ተብሎ ውድቅ ለተደረገባቸው ሌሎች ተከሳሾችም ጭምር ተፈጻሚነት አለው፡፡

በተመሣሣይ የወንጀል ህግ ድንጋጌ ጥፋተኛ ተብለውና በወንጀሉ የነበራቸው ተሣትፍ እና ሌሎች ግላዊ ሁኔታዎች ተመሣሣይ ሆኖ በመገኘቱ ተመሣሣይ የሆነ የቅጣት ውሣኔ የተላለፈባቸው ሰዎች፣ የአንደኛው የሰበር አቤቱታ የሚጣራ የህግ ነጥብ ያለው መሆኑ ተገልጾ ለሰበር ችሎት ሰለቀረበና በውሣኔው ላይ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት መሆኑ ተገልጾ በሚሰጠው ፍርድ ተጠቃሚ የሚሆንበት የሌላኛው የሰበር አቤቱታ የሰበር አጣሪ ችሎት ለሰበር አያስቀርብም ተብሎ ውድቅ ስለተደረገበት ብቻ የፍርዱ ተጠቃሚ የማይሆንበትን አግባብ መከተል በህገ መንግስቱ አንቀፅ 25 እና በወንጀል ህጉ አንቀጽ 4 የተደነገገውን የእኩልነት መርህ የሚጥስና የሰበርን መሠረታዊ ዓላማ የማያሳካ ይሆናል፡፡

የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት አንቀጽ 196 “የተፈረደባቸው ሰዎች ብዙ ሆነው አንድ ብቻ ይግባኝ ሲያቀርብ” የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን የድንጋጌው ንዑስ አንቀጽ 1 ቃል በቃል ሲነበብ “ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት ያቀረበው ይግባኝ ስለተፈረደባቸው ብዙ ሰዎች የሚመለከት ሆኖ ይግባኝ ያለው ግን የተፈረደበት አንድ ሰው ብቻ በሆነ ጊዜ ከዚህ በታች የተመለከተው ሲሆን ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሚሰጠው ፍርድ ይግባኝ ያላሉትም ሰዎች ይግባኝ እንዳሉ ተቆጥሮ ይፈጸምላቸዋል ለማለት የሚቻለው፤ /ሀ/ በይግባኝ የተሰጠው ፍርድ ይግባኝ ባዩን የሚጠቅም በሆነ ጊዜና /ለ/ ተከሳሾች ይግባኝ ቢሉ ኖሮ በፍርድ እነርሱም ሊጠቀሙ ይችሉ ነበር የሚያሰኝ ሆኖ ሲገኝ ነው” የሚል ይሁንታ ያለው ነው፡፡

ይህንን ድንጋጌ አሁን ላለው የሰበር ስርዓት ለመጠቀም ካለው የሰበር ችሎት አደራጃጀትና አሰራር ጋር  በሚጣጣምና የሰበርን መሰረታዊ ዓላማ ሊያሳካ በሚችል መንገድ መተርጎምና ስራ ላይ ማዋል ይጠይቃል፡፡ ብዙ ተከሳሾች በአንድ ወንጀል የወንጀል ስራው ተካፋይና ግብረ አበር ሆነዋል ተብለው ክስ ቀርቦባቸውና፣ ጉዳዩን በመጀመሪያ ባየው ፍርድ ቤት እና በይግባኝ ባየው ፍርድ ቤት ወይም ይግባኝ ሰሚ ችሎት የተሰጠው የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት አለበት በማለት አንደኛው ተከሳሽ የሰበር አቤቱታ አቅርቦ፣ አቤቱታው ለሰበር ችሎት ያስቀርባል ተብሎ በሰበር ችሎት ታይቶ፣ ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ ወይም በይግባኝ አይቶ ውሳኔ የሰጠው ፍ/ቤት የጥፋተኝነት ወይም የቅጣት ውሳኔ ወይም የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔው መሰረታዊ ህግ ስህተት አለበት ተብሎ ከተሻረ፣ ከተሻሻለ ወይም ከተለወጠና የሰበር ችሎት በመሻር፣  በማሻሻል ወይም በመለወጥ የሰጠው ውሳኔ የሰበር አቤቱታ ያላቀረቡትን ሌሎች በአንድ ጉዳይ የተከሰሱ ሰዎችን የሚጠቅም ሆኖ በተገኘ ጊዜ፣ ሰዎቹ ፍርዱን በመቃወም የሰበር አቤቱታ ባያቀርቡም ሰበር ችሎት በሰጠው ውሳኔ ወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 196 ንዐስ አንቀጽ 1 መሰረት ተጠቃሚ እንደሆኑ በሚያደርግ አግባብ ድንጋጌው መተርጎምና ስራ ላይ መዋል አለበት፡፡

በአንድ ወንጀል አድራጎት በወንጀል ህግ ስለወንጀል ተካፋይነት አድራጊነት ወይም ስለግብረአበርነት በተደነገጉት መሰረት በአንድ ላይ ፈጽመዋል ተብለው ክስ ከቀረበባቸው ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ ባየውና በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ የተወሰነባቸው ሰዎች ብዙ ሰዎች ሁሉም በግላቸው የሰበር አቤቱታ አቅርበው የሰበር መዝገብ አስከፍተው ከፊሎቹ ያቀረቡት የሰበር አቤቱታና ያስከፈቱት የሰበር መዝገብ በሰበር ችሎት የሚቀርብ መሠረታዊ የህግ ስህተት ጭብጥ የለውም ተብሎ በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 22 መሠረት በሰበር አጣሪ ችሎት ውድቅ ቢደረግና ቢዘጋ የከፊሎቹ ወይም አንደኛው ተከሳሽ ያቀረበው የሰበር አቤቱታ በሰበር የሚጣራ መሠረታዊ የህግ ጭብጥ አለው ተብሎ ለሰበር ችሎት ቀርቦ የሰበር ችሎቱ የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኃላ የጥፋተኝነት ውሣኔውን ወይም የቅጣት ውሳኔውን ወይም የጥፋተኛነትና የቅጣት ውሣኔውን መሠረታዊ የህግ ስህተት አለበት በማለት የሰበር ችሎት ከሻረው፣ ካሻሻለው ወይም ከለወጠውና ውሳኔው የሰበር አቤቱታ አቅርበው የሰበር ማጣሪያ ችሎት የሚጣራ መሠረታዊ የህግ ስህተት ጭብጥ የለውም ብሎ አቤቱታውን ውድቅ ያደረገባቸውን ሰዎች የሚጠቅም ሆኖ በተገኘ ጊዜ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነሥርዓት ህግ ቁጥር 196 ንዐስ አንቀፅ 1 ድንጋጌ ተፈፃሚ መሆን ይገባዋል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 101056 ቅጽ 18፣[2] ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 25፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 196

የዋስትና መብት አወሳሰን

በመርህ ደረጃ የተሻረ ሕግ ተፈፃሚነት የሌለው ሲሆን በተሻረ ሕግ ክስ ማቅረብ ደግሞ የመርሁ ልዩ ሁኔታ ነው፡፡ የተሻረውም ሕግ ተጠቅሶ በተከሳሹ ላይ ክስ የሚቀርበው ወንጀሉ ተሰርቷል በተባለ ጊዜ ሕጉ ሥራ ላይ ስለነበርና ተከሣሹም ያውቀዋል ተብሎ ስለሚገመትና በሚያውቀው ሕግ መሠረት መከራከር እንዳለበት የሕግ መርህ /Rule of legality/ ስለሚያስገድድ ነው፡፡ ከዚህም መገንዘብ የሚቻለው የተሻረው ሕግ የሚጠቀሰው ተከሳሹ ክርክሩን በአግባቡ ለመምራት እንዲያስችለው እንጂ ከዚህ ያለፈ ውጤት የሌለውና መጨረሻም ላይ ቅጣት የሚወሰነው ሥራ ላይ ባለ ሕግ ተመስርቶ መሆኑን ነው፡፡

የዋስትና ጉዳይ በዋናነት የሚታየው ቅጣትን መሠረት አድርጎ ነው፡፡ ተከሳሽ የተከሰሰው የዋስትና መብት በሚከለክል ድንጋጌ ቢሆንም ድንጋጌው የሚጠቀሰው ክርክሩን በአግባቡ ለመምራት ታስቦ እንደሆነ ሕጉ ይዞት የተነሳውን ዓላማ መገንዘብ ከተቻለ የዋስትናው ጉዳይ መታየት የሚገባው ሊወሰንበት ከሚችለው ቅጣት አኳያ መሆን እንዳለበት ይታመናል፡፡ ክርክሩ እልባት ካገኘ በኋላ ተከሳሹ የሚቀጣው በአዲሱ ሕግ መሠረት እንደሆነ ከወዲሁ በግልጽ መገንዘብ ከተቻለ ክርክሩ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በእሥር ይቆይ ማለት ሕግ አውጭው የዋስትና መብት ሊከለክላቸው ያልፈለገውን ተከሣሾች የዋስትና መብት እንደመከልከል የሚቆጠርና ሕጉም የታለመለትን ዓላማና ግብ እንዳይመታ የሚያደርግ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 34077 ቅጽ 7[3]

[1] አመልካች አቶ ሰለሞን ደሣለኝ እና ተጠሪ የደቡብ ክልል ዐ/ህግ ግንቦት 07 ቀን 2006 ዓ.ም.

[2] አመልካች አቶ አይሸሽም ገብሬ እና ተጠሪ የፌደራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሐምሌ 30 ቀን 2007 ዓ.ም.

[3] አመልካች አቶ ሰይድ ይመር እና ተጠሪ የአማራ ክልል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መጋቢት 9 ቀን 2000 ዓ.ም.


Filed under: Articles, Case Comment
Viewing all 139 articles
Browse latest View live